TIKVAH-ETHIOPIA
የታሰሩት የምክር ቤት አባላት የት ናቸው ? በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተያዙ የም/ቤት አባላት ታስረውበት ከነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የማቆያ ቦታ እንደሌሉ እና ያሉበትን ቦታ ማወቅ እንዳልቻሉ ከጠበቆቻቸው አንዱ ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ…
#EHRC
አዋሽ አርባ ላይ ታስረው የሚገኙ አብዛኞቹ እስረኞች ለእስር የተዳረጉት #በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ጨምሮ 5 የኮሚሽኑ ባለሙያዎች የሚገኙበት ቡድን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በቁጥጥር ሥር ውለው አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኘው የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙትን ታሳሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ጎብኝቷል።
እነዚህ ታሳሪዎች ፦
- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣
- የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣
- የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ካሳ ተሻገር፤
- ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ፤
- የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባል አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ አቶ በለጠ ጌትነት፤
- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ በኃላፊነት ይሠሩ የነበሩት አቶ ከፋለ እሱባለውን ጨምሮ በአጠቃላይ 53 ወንድ እስረኞች ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማና ከአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በተለያየ ጊዜ ተይዘው ከነሐሴ 15 ቀን እስከ ነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ የሚገኝ ጊዜያዊ / መደበኛ ያልሆነ ማቆያ ጣቢያ የተወሰዱ ናቸው፡፡
ኮሚሽኑ በተለመደው አሠራሩ መሠረት ታሳሪዎቹን ለብቻቸው አነጋግሯል፣ ቦታውን ጎብኝቷል እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የፖሊስ ኃላፊዎች አነጋግሯል፡፡
የፖሊስ ኃላፊዎች ለኮሚሽኑ እንደገለጹት ፤ ታሳሪዎችን ወደዚህ ጊዜያዊ ማቆያ ጣቢያ ማምጣት ያስፈለገው አዲስ አበባ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ማቆያ ጣቢያ ላይ ከፍተኛ መጣበብ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ታሳሪዎች ምን አሉ ?
እጅግ አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ብሔራቸው #አማራ፣ እምነታቸው ኦርቶዶክስ ክርስቲያን መሆኑንና ለእስር የተዳረጉት ደግሞ #በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
ከፊሎቹ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተያዙበትና ቤታቸው በተበረበረበት ወቅት በራሳቸውና በቤተሰብ አባል ላይ ድብደባ፣ ብሔር ተኮር ስድብ፣ ማጉላላት፣ ዛቻና ማስፈራራት እንደደረሰባቸው ሆኖም በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ከሆነ በኋላ የተፈጸመ ድብደባ ወይም አካላዊ ጥቃት አለመኖሩን አመልክተዋል።
ከፊሎቹ በተለይም ከአማራ ክልል ተይዘው የመጡ ሰዎች ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው የት እንዳሉ እንኳን እንደማያውቁ አስረድተዋል።
ታሳሪዎቹ የአዋሽ አርባ አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ሙቀት ያለው በመሆኑና ከአካባቢው የአየር ጠባይ እንዲሁም ቦታው የወታደራዊ ካምፕ እንጂ መደበኛ የተጠርጣሪዎች ማቆያ ስፍራ ስላልሆነ ለጤንነታቸው፣ ለደኀንነታቸውና ለሕይወታቸው ሥጋት እንዳላቸው፣ አልባሳትን ጨምሮ ከቤተስብ የሚፈልጉትን አቅርቦት ለማግኘት እንዳልቻሉ፣ ከፊሎቹ በሥራቸውም ሆነ በግል ሕይወታቸው ፈጽሞ በፖለቲካ ነክ ጉዳይ ተሳትፎ እንደሌሉና እንዴት ለእስር እንደበቁ መገረማቸውንና መደንገጣቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ ከፖሊስ ኃፊዎች ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን በእስር ወቅት ተፈጽመዋል ስለተባሉ የሥነ ምግባር ጥሰቶች ተገቢው ማጣራት እንዲደረግ፣ ታሳሪዎቹ ከቤተሰብ ለሚፈልጉት አቅርቦት አዲስ አበባ በሚገኘው የፖሊስ ቢሮ አማካኝነት እንዲመቻች፣ ከቤተስብ መገናኛ ስልክና ጉብኝት ለሚፈልጉም በአፋጣኝ እንደሚመቻች መግባባት ላይ ተደርሷል።
(ከኢሰመኮ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
አዋሽ አርባ ላይ ታስረው የሚገኙ አብዛኞቹ እስረኞች ለእስር የተዳረጉት #በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ጨምሮ 5 የኮሚሽኑ ባለሙያዎች የሚገኙበት ቡድን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በቁጥጥር ሥር ውለው አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኘው የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙትን ታሳሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ጎብኝቷል።
እነዚህ ታሳሪዎች ፦
- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣
- የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣
- የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ካሳ ተሻገር፤
- ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ፤
- የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባል አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ አቶ በለጠ ጌትነት፤
- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ በኃላፊነት ይሠሩ የነበሩት አቶ ከፋለ እሱባለውን ጨምሮ በአጠቃላይ 53 ወንድ እስረኞች ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማና ከአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በተለያየ ጊዜ ተይዘው ከነሐሴ 15 ቀን እስከ ነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ የሚገኝ ጊዜያዊ / መደበኛ ያልሆነ ማቆያ ጣቢያ የተወሰዱ ናቸው፡፡
ኮሚሽኑ በተለመደው አሠራሩ መሠረት ታሳሪዎቹን ለብቻቸው አነጋግሯል፣ ቦታውን ጎብኝቷል እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የፖሊስ ኃላፊዎች አነጋግሯል፡፡
የፖሊስ ኃላፊዎች ለኮሚሽኑ እንደገለጹት ፤ ታሳሪዎችን ወደዚህ ጊዜያዊ ማቆያ ጣቢያ ማምጣት ያስፈለገው አዲስ አበባ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ማቆያ ጣቢያ ላይ ከፍተኛ መጣበብ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ታሳሪዎች ምን አሉ ?
እጅግ አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ብሔራቸው #አማራ፣ እምነታቸው ኦርቶዶክስ ክርስቲያን መሆኑንና ለእስር የተዳረጉት ደግሞ #በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
ከፊሎቹ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተያዙበትና ቤታቸው በተበረበረበት ወቅት በራሳቸውና በቤተሰብ አባል ላይ ድብደባ፣ ብሔር ተኮር ስድብ፣ ማጉላላት፣ ዛቻና ማስፈራራት እንደደረሰባቸው ሆኖም በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ከሆነ በኋላ የተፈጸመ ድብደባ ወይም አካላዊ ጥቃት አለመኖሩን አመልክተዋል።
ከፊሎቹ በተለይም ከአማራ ክልል ተይዘው የመጡ ሰዎች ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው የት እንዳሉ እንኳን እንደማያውቁ አስረድተዋል።
ታሳሪዎቹ የአዋሽ አርባ አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ሙቀት ያለው በመሆኑና ከአካባቢው የአየር ጠባይ እንዲሁም ቦታው የወታደራዊ ካምፕ እንጂ መደበኛ የተጠርጣሪዎች ማቆያ ስፍራ ስላልሆነ ለጤንነታቸው፣ ለደኀንነታቸውና ለሕይወታቸው ሥጋት እንዳላቸው፣ አልባሳትን ጨምሮ ከቤተስብ የሚፈልጉትን አቅርቦት ለማግኘት እንዳልቻሉ፣ ከፊሎቹ በሥራቸውም ሆነ በግል ሕይወታቸው ፈጽሞ በፖለቲካ ነክ ጉዳይ ተሳትፎ እንደሌሉና እንዴት ለእስር እንደበቁ መገረማቸውንና መደንገጣቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ ከፖሊስ ኃፊዎች ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን በእስር ወቅት ተፈጽመዋል ስለተባሉ የሥነ ምግባር ጥሰቶች ተገቢው ማጣራት እንዲደረግ፣ ታሳሪዎቹ ከቤተሰብ ለሚፈልጉት አቅርቦት አዲስ አበባ በሚገኘው የፖሊስ ቢሮ አማካኝነት እንዲመቻች፣ ከቤተስብ መገናኛ ስልክና ጉብኝት ለሚፈልጉም በአፋጣኝ እንደሚመቻች መግባባት ላይ ተደርሷል።
(ከኢሰመኮ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
👍1.97K😢386👎248❤204🕊27🙏25👏21🥰11😱9
#አማራ
ዋዜማው እና የአዲስ አመቱ አቀባበል በአማራ ክልል እንዴት ነው ?
በአማራ ክልል በቅርቡ ባጋጠመው ደም አፋሳሽ ግጭት ምክንያት የዘንድሮው አዲስ ዓመት አቀባበል ቀዝቃዛ እንደሆነ ነዋሪዎች እየገለፁ ናቸው።
ባለፉት ዓመታት የነበሩ የአዲስ ዓመት አቀባበሎችም ክልሉ ባስተናገደው አስከፊ ጦርነት ምክንያት ዜጎች በተሟላ ሰላም በዓሉን መቀበል እንዳልቻሉ የሚታወቅ ነው።
በዘንድሮው ዓመትም ባጋጠመው ጦርነት ሰላም በመራቁ የአዲስ አመት አቀባበሉ ጥላ ያጠላበት ነው።
የኢተርኔት አገልግሎት በክልሉ እንደተቋረጠ ነው።
ዛሬ ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡ የክልሉ ነዋሪዎች የበዓሉ ድባብ ቀዝቃዛ ነው ብለዋል።
የደብረታቦር ከተማ ነዋሪ ፦
" በዓሉን በተመለከተ የተለየ ነገር በከተማው አይታይም።
የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት በመቋረጡም የመልካም ምኞት መልዕክቶችን መለዋወጥ አልቻልንም። "
የደንበጫ ከተማ ነዋሪ ፦
" አካባቢው እንስሳት የሚደልቡበት አካባቢ ነው። በነበረው አለመረጋጋት እንስሳት መድለብ አልቻሉም። ከሌላ ቦታ ሄዶ የእርድ እንስሳትንም መግዛት አልተቻለም።
አጋጣሚው በአዲሱ ዓመት አቀባበል ላይ አሉታዊ ጫና ፈጥሯል። "
ሌላ የዚሁ ከተማ ነዋሪ ፦
" የዓመት በዓሉን መድረስ የሚያመላክቱ ሙዚቃዎች አይሰሙም፣ ለእርድ እንስሳት የተዘጋጄ ሰው አላየሁም። "
የቢቸና ነዋሪ ፦
" ከዚህ ቀደም በነበሩ የበዓል ዝግጅቶች የእርድ እንስሳትን ቀደም ብለው ይገዙ ነበር።
አርሶ አደሩም ሆነ የእንስሳት ነጋዴው የደህንነት ስጋት ስላደረበት እንስሳቱን ወደ ገበያ ማውጣት አልቻለም። "
የደብረ ማርቆስ ነዋሪ ፦
" በጦርነት ቆፈን ሆኖ በዓል ማክበር አይቻልም። "
የፈረስ ቤት ከተማ ነዋሪ ፦
" ሁሉም ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ወደ ሥራ ባለመግባታቸው በአዲሱ ዓመት አከባበር ላይ ከፍተኛ ጫና ተፈጥሯል። "
ይህች ከተማ በቅርብ ብርቱ ውጊያ ያስተናገደች ናት።
የደሴ ከተማ ነዋሪ ፦
" ወቅታዊ ሁኔታው በበዓሉ ድምቀት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። "
የባህርዳር ነዋሪዎች ፦
" የባሕር ዳር ከተማ የዓመት በዓል ድባቡ ብዙ ባይታይም የእንስሳት አቅርቦት አለ።
ካለፈው ዓመት ሲነፃፀር የዋጋ መጨመር ይታያል ብለዋል፡፡ "
የእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ ነዋሪ ፦
" ሰሞኑን በዋለው ገበያ የእንስሳቱም ሆነ ሌሎች ለምግብ ፍጆታ የሚውሉ ሸቀጦች ዋጋ እጅግ ጨምሯል።
ምክንያቱም ወደ ከተማዋ የሚያስገቡ መንገዶች በሙሉ ባለመከፈታቸው ሸቀጦች እንደልብ እየገቡ ባለመሆናቸው ነው፡፡ "
@tikvahethiopia
ዋዜማው እና የአዲስ አመቱ አቀባበል በአማራ ክልል እንዴት ነው ?
በአማራ ክልል በቅርቡ ባጋጠመው ደም አፋሳሽ ግጭት ምክንያት የዘንድሮው አዲስ ዓመት አቀባበል ቀዝቃዛ እንደሆነ ነዋሪዎች እየገለፁ ናቸው።
ባለፉት ዓመታት የነበሩ የአዲስ ዓመት አቀባበሎችም ክልሉ ባስተናገደው አስከፊ ጦርነት ምክንያት ዜጎች በተሟላ ሰላም በዓሉን መቀበል እንዳልቻሉ የሚታወቅ ነው።
በዘንድሮው ዓመትም ባጋጠመው ጦርነት ሰላም በመራቁ የአዲስ አመት አቀባበሉ ጥላ ያጠላበት ነው።
የኢተርኔት አገልግሎት በክልሉ እንደተቋረጠ ነው።
ዛሬ ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡ የክልሉ ነዋሪዎች የበዓሉ ድባብ ቀዝቃዛ ነው ብለዋል።
የደብረታቦር ከተማ ነዋሪ ፦
" በዓሉን በተመለከተ የተለየ ነገር በከተማው አይታይም።
የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት በመቋረጡም የመልካም ምኞት መልዕክቶችን መለዋወጥ አልቻልንም። "
የደንበጫ ከተማ ነዋሪ ፦
" አካባቢው እንስሳት የሚደልቡበት አካባቢ ነው። በነበረው አለመረጋጋት እንስሳት መድለብ አልቻሉም። ከሌላ ቦታ ሄዶ የእርድ እንስሳትንም መግዛት አልተቻለም።
አጋጣሚው በአዲሱ ዓመት አቀባበል ላይ አሉታዊ ጫና ፈጥሯል። "
ሌላ የዚሁ ከተማ ነዋሪ ፦
" የዓመት በዓሉን መድረስ የሚያመላክቱ ሙዚቃዎች አይሰሙም፣ ለእርድ እንስሳት የተዘጋጄ ሰው አላየሁም። "
የቢቸና ነዋሪ ፦
" ከዚህ ቀደም በነበሩ የበዓል ዝግጅቶች የእርድ እንስሳትን ቀደም ብለው ይገዙ ነበር።
አርሶ አደሩም ሆነ የእንስሳት ነጋዴው የደህንነት ስጋት ስላደረበት እንስሳቱን ወደ ገበያ ማውጣት አልቻለም። "
የደብረ ማርቆስ ነዋሪ ፦
" በጦርነት ቆፈን ሆኖ በዓል ማክበር አይቻልም። "
የፈረስ ቤት ከተማ ነዋሪ ፦
" ሁሉም ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ወደ ሥራ ባለመግባታቸው በአዲሱ ዓመት አከባበር ላይ ከፍተኛ ጫና ተፈጥሯል። "
ይህች ከተማ በቅርብ ብርቱ ውጊያ ያስተናገደች ናት።
የደሴ ከተማ ነዋሪ ፦
" ወቅታዊ ሁኔታው በበዓሉ ድምቀት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። "
የባህርዳር ነዋሪዎች ፦
" የባሕር ዳር ከተማ የዓመት በዓል ድባቡ ብዙ ባይታይም የእንስሳት አቅርቦት አለ።
ካለፈው ዓመት ሲነፃፀር የዋጋ መጨመር ይታያል ብለዋል፡፡ "
የእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ ነዋሪ ፦
" ሰሞኑን በዋለው ገበያ የእንስሳቱም ሆነ ሌሎች ለምግብ ፍጆታ የሚውሉ ሸቀጦች ዋጋ እጅግ ጨምሯል።
ምክንያቱም ወደ ከተማዋ የሚያስገቡ መንገዶች በሙሉ ባለመከፈታቸው ሸቀጦች እንደልብ እየገቡ ባለመሆናቸው ነው፡፡ "
@tikvahethiopia
👍796😢390❤107👎52🕊46🥰10😱8🙏8