TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሞሮኮ

እጅግ አስደንጋጭ ነው በተባለው የሞሮኮ መሬት መንቀጥቀጥ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ሞቱ።

በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ እስካሁን  ባለው 1,305 ሰዎች መሞታቸው ታውቋል።

ቢቢሲ ኒውስ ፤ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የተከሰተው 6.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ሲሆን በዚህም እጅግ በጣም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው ተብሏል።

ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው። በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።

አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።

በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲናዱ ታይተዋል።

ሞሮኮ በደረሰው አደጋ የ3 ቀን ሀዘን አውጃለች።

በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በደረሰው ጉዳት የኢትዮጵያ መሪን ጨምሮ የሀገራትና ተቋማት መሪዎች ሀዘናቸውን እና ለሞሮኮ ህዝብ ያላቸውን አጋርነት እየገለፁ ይገኛሉ።

NB. የሟቾች ቁጥር አሁን ካለውም ይጨምራል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
😢3.23K👍788178🕊145😱73🙏60🥰25👎21