#update ሀዋሳ⬇️
በሃዋሳ ከተማ ባለፉት ጊዚያት በተለያዩ ግጭቶች ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች ተጠልለው የቆዩ ተፈናቃዮች ካሳለፍነው ቅዳሜ ጀምሮ ወደ መኖሪያ ቀያቸው አየተመለሱ መሆኑ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
📌ተፋናቃዮችን ወደ ቀያቸው ከመመለስ ጎን ለጎን የእርቅ ስራ አየተሰራ ሲሆን፥ #ሰፋ ያለ #የእርቅ ፕሮግራም #በቅርቡ የሚካሄድ መሆኑንም ተሰምቷል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሃዋሳ ከተማ ባለፉት ጊዚያት በተለያዩ ግጭቶች ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች ተጠልለው የቆዩ ተፈናቃዮች ካሳለፍነው ቅዳሜ ጀምሮ ወደ መኖሪያ ቀያቸው አየተመለሱ መሆኑ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
📌ተፋናቃዮችን ወደ ቀያቸው ከመመለስ ጎን ለጎን የእርቅ ስራ አየተሰራ ሲሆን፥ #ሰፋ ያለ #የእርቅ ፕሮግራም #በቅርቡ የሚካሄድ መሆኑንም ተሰምቷል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
❤1
#update ደዴሳ⬆️
በቤኔሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ተወላጆች መካከል የነበረውን ግጭት ወደ እርቅ የሚመራ የአባቶች ሽምግልና ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በሎይጅጋንፎ ወረዳ በለው ደዴሳ ቀበሌ በቤኔሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ተወላጆች መካከል ግጭት ተፈጥሮ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ከሁለቱም ብሄሮች በኩል አስታራቂ የሃይማኖት አባቶች እና የሃገር ሽማግሌዎች በተገኙበት #የእርቅ ስነ ስርዓት ተፈጽሟል፡፡
ነገ ደግሞ #ይቅር መባባላቸውን የሚያበስረው የእርቅ ስርአት ባህሉን መሰረት አድረጎ ይከናወናል፡፡
©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በቤኔሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ተወላጆች መካከል የነበረውን ግጭት ወደ እርቅ የሚመራ የአባቶች ሽምግልና ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በሎይጅጋንፎ ወረዳ በለው ደዴሳ ቀበሌ በቤኔሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ተወላጆች መካከል ግጭት ተፈጥሮ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ከሁለቱም ብሄሮች በኩል አስታራቂ የሃይማኖት አባቶች እና የሃገር ሽማግሌዎች በተገኙበት #የእርቅ ስነ ስርዓት ተፈጽሟል፡፡
ነገ ደግሞ #ይቅር መባባላቸውን የሚያበስረው የእርቅ ስርአት ባህሉን መሰረት አድረጎ ይከናወናል፡፡
©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር🔝
በጎንደር የሰላምና እርቅ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። በአማራ እና ቅማንት ማህበረሰብ የተፈጠረውን ቁርሾ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ህዝባዊ #የሰላምና #የእርቅ ጉባኤ በጎንደር እየተካሄደ ነው፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር #ደመቀ_መኮንን እና የሐይማኖት አባቶች በተገኙበት መድረክ የሰላምና ጉባኤው በዛሬው ዕለት ሲካሄድ ይውላል፡፡
ዓላማውም በጎንደር በተለይም ማዕከላዊና ሰሜን ጎንደር ዞኖች ማንነትን መሰረት አድርገው የሚነሱ ግጭቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ #በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው፡፡
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በጎንደር የሰላምና እርቅ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። በአማራ እና ቅማንት ማህበረሰብ የተፈጠረውን ቁርሾ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ህዝባዊ #የሰላምና #የእርቅ ጉባኤ በጎንደር እየተካሄደ ነው፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር #ደመቀ_መኮንን እና የሐይማኖት አባቶች በተገኙበት መድረክ የሰላምና ጉባኤው በዛሬው ዕለት ሲካሄድ ይውላል፡፡
ዓላማውም በጎንደር በተለይም ማዕከላዊና ሰሜን ጎንደር ዞኖች ማንነትን መሰረት አድርገው የሚነሱ ግጭቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ #በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው፡፡
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia