TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዳማ ግጭት ተፈጥሮ በነበረበት ቦታ አሁን ላይ መረጋጋት አለ። ግጭቱ በተፈናቃዮች እና በአዳማ ነዋሪዎች መካከል የተፈጠረ ነው።

ይህ አጋጣሚ ተጠቅመው ግጭቱን የብሄር ግጭት ለማስመሰል በፌስቡክ የሚፃፉ ፅሁፎችን እየተመለከትን እንገኛለን ነገር ግን #ማረጋገጥ የቻልነው በአዳማ የተፈጠረው ግጭት ምንም አይነት የብሄር መልክ የያዘ ግጭት እንዳልነበረ ነው። ከዚህ ባለፈም በፌስቡክ ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ ተብሎ የሚወራው #ውሸት ነው ምንም ቤተ ክርስቲያን አልተቃጠለም።

*ስለደረሰው ጉዳት ተጨማሪ መረጃዎች እየመጡልኝ ስለሆነ አጣርቼ አሳውቃለሁ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አቶ ጌታቸው ከሀገር ወጡ??❗️

ይህ የአንጋፋው ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ዘገባ ነው...

"ሰበር ዜና-ከአዲስ አበባ ለአዋዜ የደረሰው ትኩስ ዜና። የቀድሞው ተፈሪ የብሄራዊ ስለላና ደህንነት ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ ከኢትዮጵያ #ጠፍተው ሱዳን መግባታቸው በይፋ #ተረጋገጠ። አንድ ከፍተኛ ውስጥ አዋቂ ምንጭ ምሽቱን ለአዋዜ እንደተናገሩት ከሆነ ፌደራል መንግስቱ በህግ ይፈልጋቸው የነበሩ ባለስልጣን ናቸው ጌታቸው አሰፋ።

ማዕከላዊ መንግስቱ በይፋ በህግ #ሊጠይቃቸው እና #ሊፋረዳቸው የሚፈልጋቸው ባለስልጣን ሆነው ሳሉ በትግራይ ፖሊስ ሽፋን ወደ ሱዳን እንዲወጡ አድርጓል ብለዋል ለአዋዜ። በዚህ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም።"

ጋዜጠኛ አለምነህ ጨምሮ እንደገለፀው ከሆነ እየተደረገ በሚገኘው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ አቶ ጌታቸው አሰፋ አልተገኙም። ይህም የሆነው ከሀገር በመውጣታቸው ነው ብሏል ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ።

በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን እና ሬድዮ ከምንጮች አገኘሁት ባለው መረጃ እንዲህ ብሎ በሰበር ዜናው ዘግቧል⬇️

"የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው የቀድሞ የደህንነት ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ ወደ ሱዳን #መሸሻቸው ተነገረ።"

◾️ውድ የተከባራቹ የቻናላችን ቤተሰቦች ይህን ዜና #እስካሁን ድረስ ከሌሎች የመንግስትም ሆነ የግል የሚዲያዎች #ማረጋገጥ አልተቻለም።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
የእርቅ ኮሚቴ አባላት ታፍነው ተወሰዱ‼️

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር እና በመንግሥትን መካከል የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የግንባሩን ወታደሮች #ለመቀበል ወደ #ቄለም_ወለጋ አቅንተው የነበሩ ከሦስት ያላነሱ የአስታራቂ ኮሚቴ አባላት #ታፍነው መወሰዳቸው ተሰምቷል።

የእርቅ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት አባ ገዳ #በየነ_ሰንበቶ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት የኮሚቴው አባላት የሆኑ ሁለት አባ ገዳዎች እና አንዲት ሴት በቄለም ወለጋ #አንፊሎ ተብሎ ከሚጠራ ስፍራ ታፍነው እንደተወሰዱ ተናግረዋል።

አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ''ለማግባባት ወጣ እንዳሉ ነው ታፍነው የተወሰዱት፤ ክፉ ነገር #እንደማይገጥማቸው እርግጠኛ ነኝ። ይህንም ችግር በቅርቡ እንፈታዋለን'' ሲሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

''ብዙ ፈተናዎች እንደሚኖሩን እየወቅን ነው እርቅ ወደማውረዱ የገባነው። እርቅ ለማምጣት ነው እየሰራን ያለነው። ሰላምም ይሰፍናል። የሚያጋጥሙን ችግሮች ወደ ኋላ አያሰቀሩንም'' ሲሉም ጥረታቸውን በዚህ ምክንያት እንደማያቋርጡም ተናግረዋል።

ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ቢቢሲ ያነጋገረው የየኮሚቴው ፀሃፊ #ጀዋር_መሃመድም የእርቅ ኮሚቴ አባላት ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ተናግሯል።

''የገጠመ ችግር አለ። በተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ከኮሚቴው አባላት ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ለህዝቡ መግለጫ እንሰጣለን'' ሲል ጀዋር ገልጿል።

ጀዋር ሃሙስ ምሽት ላይ በፌስቡክ ገጹ ላይ ታፍነው ተወስደዋል ያላቸውን አራት ሰዎች ከስም ዝርዝራቸው ጋር አውጥቷል። ታፍነዋል ተወስደዋል የተባሉት ሰዎች የት እንዳሉ ምንም አይነት መረጃ እንደሌላቸው ተናግሯል።

በተመሳሳይ መልኩ በምዕራብ ወለጋ መነ ሲቡ ወረዳ የቴክኒክ አባላቱ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ከነዋሪዎች ተሰምቷል። ተፈጸሟል ስለተባለው ድብደባ ግን ከቴክኒክ ኮሚቴው አባላት #ማረጋገጥ አልተቻለም።

የእርቅ ኮሚቴ አባላቱን ማን አፈናቸው?

የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት አባ ገዳ በየነ ሰንበቶም ሆኑ የኮሚቴው ፀሃፊ ጀዋር መሃመድ የእርቅ ኮሚቴውን አባላት ያፈነው ኃይል ይህ ነው በማለት በስም ከመጥቀስ #ተቆጥበዋል

ጀዋር የአባላቱን መታፈን ይፍ ባደረገበት ጽሁፍ ''እየደረሰብን ያለውን #ስቃይ ሁሉ በሆዳችን ይዘን እየሄድን ነው። አሁን ግን የህይወት ጉዳይ ስለሆነ መናገር አለብን። አባ ገዳዎች፣ እናቶች እና የሃገር ሽማግሌዎች ለሃገር ሰላም እና እርቅ ለማውረድ ነው የሚደክሙት እንጂ ምንም በደል አልፈጸሙም። በአስቸኳይ እንዲለቀቁን እንጠይቃለን'' ሲል በፌድቡክ ገጹ ላይ አስፍሯል።

ከዚህ ቀደምም በምዕራብ ኦሮሚያ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶ/ር ደለሳ ቡልቻ ለሁለት ቀናት ታፍነው ከቆዩ በኋላ መለቀቃቸው ይታወሳል። ዶ/ር ደለሳ የገጠማቸውንና ማን እንዳፈናቸው ለመናገር ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኙ ባንኮች በተዘረፉበት ወቅትም የባንክ ሰራተኞችም ታፍነው ተወስደው እንደነበረ ይታወሳል።

ምንጭ፦ BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የባለ ዕድለኛ የዕጣ ዝርዝር ላይ ስማችሁን ማግኘት ያልቻላሁ / ባለዕድለኛ #መሆን #አለመሆናችሁን ማረጋገጥ የምትፈልጉ ፦ - በቅድሚያ የPDF ፋይሉን https://tttttt.me/tikvahethiopia/74809 አውርዱ (Download) - በመቀጠልም ከላይ በምስሉ የሚታየውን የመፈለጊያውን ምልክት ተጫኑ፤ - በመጨረሻም ስማችሁን በማስገባት የመፈለጊያውን ምልክት…
Addis Lissan Hidar 8-2015 .pdf
52.3 MB
የ20/80 እና የ40/60 የቤት ባለዕድለኞች የስም ዝርዝር በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ላይ (በልዩ ዕትም) ታትሞ ወጥቷል።

ከላይ የተያያዘው " የአዲስ ልሳን " ጋዜጣ ቅጂ (ሶፍት ኮፒ) ነው።

ከላይ የተያያዘውን " 52.3 MB " PDF ፋይል በማውረድና በመክፈት የመፈለጊያ ምልክቷን በመጫን ስምዎትን በአማርኛ / በእንግሊዝኛ በማስገባት ስምዎት በጋዜጣው ላይ ታትሞ ስለመውጣቱ #ማረጋገጥ ይችላሉ።

Credit : Addis Lissan

@tikvahethiopia
👍1.81K👎341🙏191169😢118🕊106😱67
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር  ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን መቼ ለመስጠት እቅድ ይዟል ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰውና በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተሰራጨ አንድ ደብዳቤ የዚህ ዓመት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ሊሰጡ #የታቀደበትን ጊዜ ያመለክታል።

የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከታቸው የትምህርት ሚኒስቴር አካላት #ማረጋገጥ ችሏል።

በዚህ መሰረት ፦

1ኛ. በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት #በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ኘሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀውን ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደትም እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስመቅጧል።

2ኛ. በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 /2015 እስከ ሐምሌ 13 /2015 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።

3ኛ. የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

በተጨማሪም እንደ አገር ዓመታዊ የትምህርት ካላንደር ከ2016 ጀምሮ ለማስተካከል ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚሁ ማዕቀፍ አንዲያስተካክሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።

ከሀገር አቀፍ ፈተናዎች ጋር በተያያዘ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ የተለያዩ #ያልተረጋገጡ መረጃዎችን እየሰሙ አለመረጋጋት ውስጥ መግባታቸውን ሲገልፁልን ነበር ፤ በቀጣይም ትምህርት ሚኒስቴር / የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የሚሰጡትን ትክክለኛ መረጃ #ብቻ እንድትከታተሉ ፤ በቀረው አጭር ጊዜም ዝግጅታችሁን ታጠናክሩ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን።

(ከላይ የተያያዘው ደብዳቤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከተው አካል #ትክክለኝነቱን ያረጋገጠው ነው።)

@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
👍1.38K162👎100😢39😱29🕊22🥰19🙏19