TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከአዲስ አበባ ያመለጠው የኮቪድ-19 ታማሚ!

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ሰባት (7) መሆናቸውን ገልጿል።

ከነዚህ ሰባት (7) ሰዎች መካከል አንደኛው ከአዲስ አበባ ከተማ #አምልጦ የተያዘ እንደሆነ ቢሮው በዛሬው ዕለታዊ መግለጫው ጠቁሟል።

ይህ ከአዲስ አበባ ከተማ አምልጦ የተያዘው ግለሠብ #በትላንትናው ዕለት የጤና ሚኒስቴር አዲስ በቫይረሱ መያዛቸው ካረጋገጠው 61 ሰዎች ውስጥ አንደኛው ነው።

ግለሠቡ በጉራጌ ዞን ማረቆ ወረዳ ላይ ተይዞ እዛው በይቶ ማቆያ እንዲቆይ ተደርጓል። ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው 30 ያህል ሰዎች ተለይተው በማቆያ ውስጥ እንደሚገኙ የክልሉ ጤና ቢሮ አሳውቋል።

በነገራችን ላይ በደ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግስት ባለፉት 24 ሰዓት 76 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በቫይረሱ የተያዘ ሰው #አልተገኘም። እስካሁን በአጠቃላይ ለ1,072 ሰዎች ምርመራ ተደርጓል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
" ... መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉት 10 የከባድ ውንብድና ፍርደኛ ታራሚዎች ናቸው " - ቃሊቲ ማረሚያ ቤት

ከቃሊቲ ማረሚያ መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ነበሩ የተባሉ ታራሚዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰምቷል።

ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት  መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉር የከባድ ውንብድና ወንጀል ፍርደኛ ታራሚዎች መሆናቸው ተነግሯል።

ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጥበቃና የደኅንነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ድሪባ ሰንበታ ለኤፍ ቢ ሲ የሰጡት ቃል ፦

" ትናንት ሌሊት 10 ሰዓት ከ30 ላይ መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉ 10 የከባድ ውንብድና ፍርደኛ ታራሚዎች ላይ ማረሚያ ቤቱ ባደረገው ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ለማምለጥ ሙከራ ካደረጉ ፍርደኞች መካከል ከዚህ በፊት #አምልጦ ከጣልያን ሀገር በኢንተርፖል ተይዞ የመጣ ታራሚ ይገኝበታል።

ሌሎችም በተደጋጋሚ ከጤና ጣቢያ ፣ከመኪና ላይ ጭምር ለማምለጥ ሞክረው የተያዙ ፍርደኞች አሉ።

ማረሚያ ቤቱ  ዛሬ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ቀጠሮ የነበራቸው ታራሚዎችን አጅቦ በማቅረብ መደበኛ ስራውን ሲሰራ ውሏል።

ታራሚዎቹ  ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠቡ ተገቢ የሆነ  የክትትልና የቁጥጥር ስራው ይቀጥላል። "

Credit : #FBC

@tikvahethiopia
👍1.74K👎333187😱131🥰52😢38🕊31🙏27😭1