TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba📍 በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ፤ የቦሌ ክ/ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ሃላፊ በህገ ወጥ ንግድ ምክንያት የታሽገን የንግድ ቤት እከፍትልሃለሁ በሚል 100 ሺ ብር #ጉቦ ሲቀበል እጅ ከፍንጅ መያዙን የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ የንግድ ፅ/ቤት ሃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ ታሽጎ የነበረን የንግድ ቤት በህገ ወጥ መንገድ ለመክፈት ተስማምቶ…
#ተጨማሪ
የቦሌ ክ/ ከተማ ንግድ ቢሮ ኃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ 100 ሺህ ብር ጉቦውን የተቀበሉት ታሽጎ የነበረውን " አቤኔዘር የተሽከርካሪ እጥበት አገልግሎት ድርጅት " ን አስከፍታለሁ ፤ የንግድ ፈቃዱንም እንዲታደስ አደርጋለሁ በማለት ነው።
የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳለው ከሆነ፤ የድርጅቱ ባለንብረት በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ታሽጎ የነበረው ድርጅታቸው እንዲከፈትና ንግድ ፈቃድ እንዲታደስላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ መነሻ በማድረግ የስራ ኃላፊው 100,000 ብር ጉቦ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
በኃላም 22 ጎላጎል ህንጻ በሚገኘው ካፌ ውስጥ ብሩን ሲቀበሉ #እጅ_ከፍንጅ ተይዘዋል ፤ አሁን ላይም ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።
#AMN
@tikvahethiopia
የቦሌ ክ/ ከተማ ንግድ ቢሮ ኃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ 100 ሺህ ብር ጉቦውን የተቀበሉት ታሽጎ የነበረውን " አቤኔዘር የተሽከርካሪ እጥበት አገልግሎት ድርጅት " ን አስከፍታለሁ ፤ የንግድ ፈቃዱንም እንዲታደስ አደርጋለሁ በማለት ነው።
የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳለው ከሆነ፤ የድርጅቱ ባለንብረት በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ታሽጎ የነበረው ድርጅታቸው እንዲከፈትና ንግድ ፈቃድ እንዲታደስላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ መነሻ በማድረግ የስራ ኃላፊው 100,000 ብር ጉቦ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
በኃላም 22 ጎላጎል ህንጻ በሚገኘው ካፌ ውስጥ ብሩን ሲቀበሉ #እጅ_ከፍንጅ ተይዘዋል ፤ አሁን ላይም ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።
#AMN
@tikvahethiopia
👍1.05K👎141👏73😢35🥰33😱33❤18