" ከአፍጥርና ከፆም ሰዓታት በኋላ ደም በመለገስ የደም ሕክምና የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች እንታደግ " - ደም ባንክ
በተያዘው የጾም ወቅት በቂ ደም ከማግኘት አንፃር ውስነነት መኖሩን የኢትዮጵያ ደም እና ኅብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ባንኩ በዚህ ወቅት በቂ ደም እያገኘ አለመሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ታዬ ለፋብኮ ተናግረዋል።
#ሕይወትን_ማትረፍ ከፆሙ ዓላማ አንፃር ያለው ፋይዳ ትልቅ ስለሆነ ከአፍጥር እንዲሁም ከፆም ሰዓታት በኋላ ደም በመለገስ የደም ሕክምና የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ለመታደግ ሕብረተሰቡ በንቃት ደም እንዲለግስም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ደም የሚያስፈልጋቸውን ዜጎች ሕይወት ለመታደግ በተንቀሳቃሽ እና በቋሚ ቦታዎች እንዲሁም በሥራ ቀናት በትምህርት ቤቶች፣ መንግሥታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት በመዘዋወር የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ቅዳሜ ቅዳሜ አደባባይ ላይ ድንኳን በመትከል የበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በመቀስቀስ እና እሁድ በቤተ እምነቶች የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተከናነ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
#ኤፍቢሲ
More : @tikvahethmagazine
በተያዘው የጾም ወቅት በቂ ደም ከማግኘት አንፃር ውስነነት መኖሩን የኢትዮጵያ ደም እና ኅብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ባንኩ በዚህ ወቅት በቂ ደም እያገኘ አለመሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ታዬ ለፋብኮ ተናግረዋል።
#ሕይወትን_ማትረፍ ከፆሙ ዓላማ አንፃር ያለው ፋይዳ ትልቅ ስለሆነ ከአፍጥር እንዲሁም ከፆም ሰዓታት በኋላ ደም በመለገስ የደም ሕክምና የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ለመታደግ ሕብረተሰቡ በንቃት ደም እንዲለግስም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ደም የሚያስፈልጋቸውን ዜጎች ሕይወት ለመታደግ በተንቀሳቃሽ እና በቋሚ ቦታዎች እንዲሁም በሥራ ቀናት በትምህርት ቤቶች፣ መንግሥታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት በመዘዋወር የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ቅዳሜ ቅዳሜ አደባባይ ላይ ድንኳን በመትከል የበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በመቀስቀስ እና እሁድ በቤተ እምነቶች የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተከናነ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
#ኤፍቢሲ
More : @tikvahethmagazine
❤316👍231👎48🤔17🕊17😢10😱2🙏2
#ነዳጅ
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በማደያዎች የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የማካሄድ የሙከራ ትግበራ ሥራ መጀመሩን አሳውቋል።
ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የዲጂታል የነዳጅ ግብይት ይጀመራል ተብሏል።
ዛሬ በአዲስ አበባ ለሙከራ የተጀመረው የዲጂታል ግብይት በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
ግብይቱ በዲጂታል መሆኑ ምርት እንዳይባክን እና የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር እንደሚያደርግ ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው።
የነዳጅ ግብይቱ በ #ቴሌብር አማራጭ የሚከናወን ነው የተባለ ሲሆን በዚህ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ሁሉም የመንግስት እና የግል ተሽከርካሪዎች ቁጥጥር ይደረግባቸዋል ተብሏል።
ሚኒስቴሩ በቅርቡ የትራንስፖርት ትኬት በዲጂታል እንደሚጀመር አሳውቋል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በማደያዎች የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የማካሄድ የሙከራ ትግበራ ሥራ መጀመሩን አሳውቋል።
ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የዲጂታል የነዳጅ ግብይት ይጀመራል ተብሏል።
ዛሬ በአዲስ አበባ ለሙከራ የተጀመረው የዲጂታል ግብይት በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
ግብይቱ በዲጂታል መሆኑ ምርት እንዳይባክን እና የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር እንደሚያደርግ ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው።
የነዳጅ ግብይቱ በ #ቴሌብር አማራጭ የሚከናወን ነው የተባለ ሲሆን በዚህ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ሁሉም የመንግስት እና የግል ተሽከርካሪዎች ቁጥጥር ይደረግባቸዋል ተብሏል።
ሚኒስቴሩ በቅርቡ የትራንስፖርት ትኬት በዲጂታል እንደሚጀመር አሳውቋል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
👍819👎209❤84🥰20😱20🙏13🕊9😢8