TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
በኢትዮጵያ ምን ያህል መስማት የተሳናቸው ዜጎች ይኖራሉ?
በወቅታዊ ጥናት ላይ ተሞርክዞ የቀረበ መረጃ ባይኖርም እንደማሳያ የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ፣ የዓለም የጤና ድርጅትና የዩኒሴፍ ጥናቶችን መመልከት ይቻላል፡፡
የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ በ2005 ዓ.ም በሰራው ዳሰሳ ኢትዮጲያ ከህዝብ ቁጥሯ 3 በመቶ የሚሆነው አካል ጉዳተኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ከዚህ ውስጥም 20 በመቶ ሚሆኑት (720 ሺ) መስማት የተሳናቸው መሆናቸውን ይጠቅሳል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ በ2003 ዓ.ም ባወጡት ሪፖርት ከኢትዮጲያ ከህዝብ ቁጥሯ 15 ሚሊዮን ዜጎቿ (17.6 በመቶ) አካል ጉዳተኛ መሆናቸውን ገልጾ፤ ከዚህ ውስጥም 20 በመቶ ሚሆኑት (3.5 ሚሊዮን በላይ) መስማት የተሳናቸው ይላል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በ2013 ዓ.ም ባወጣው ቁጥራዊ ማስረጃ (Fact Sheet on Deafness and Hearing loss) ላይ ደግሞ በኢትዮጵያ ከ5 ሚሊዮን በላይ መስማት የመስማት ችግር ያለባቸው ዜጎች መኖራቸውን ይጠቅሳል።
ዩኒሴፍ ከሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር በ2008 ዓ.ም በሰራው ዳሰሳ የአካል ጉዳተኛ ዜጎች ከአጠቃላይ የህዝብ ቁጥሩ 9.3 በመቶ (7.8 ሚሊዮን) መሆኑን ያስቀምጣል፡፡ ከላይ በሁለቱም ጥናቶች የተወሰደውን ስሌት ተጠቅመን 20 በመቶዎቹ መስማት የተሳናቸው ናቸው ብንል ከ1.5 ሚሊዮን በላይ መስማት የተሳናቸው ዜጎች ይኖራሉ።
#ማስታወሻ፡ በተለያየ ጊዜያት የተሰሩትና ማግኘት የቻልናቸው የጥናት ውጤቶች ግኝት በጣም የተራራቁ ቢሆንም ለማሳያ ያክል የቀረቡ ናቸው። ቁጥራዊ መረጃዎቹ ወቅታዊ መረጃን ገላጭ አይደሉም፡፡ ተጨማሪ መረጃዎች ካሎት @RWethiopia ላይ ያካፍሉን
#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ
@tikvahethiopia
በወቅታዊ ጥናት ላይ ተሞርክዞ የቀረበ መረጃ ባይኖርም እንደማሳያ የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ፣ የዓለም የጤና ድርጅትና የዩኒሴፍ ጥናቶችን መመልከት ይቻላል፡፡
የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ በ2005 ዓ.ም በሰራው ዳሰሳ ኢትዮጲያ ከህዝብ ቁጥሯ 3 በመቶ የሚሆነው አካል ጉዳተኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ከዚህ ውስጥም 20 በመቶ ሚሆኑት (720 ሺ) መስማት የተሳናቸው መሆናቸውን ይጠቅሳል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ በ2003 ዓ.ም ባወጡት ሪፖርት ከኢትዮጲያ ከህዝብ ቁጥሯ 15 ሚሊዮን ዜጎቿ (17.6 በመቶ) አካል ጉዳተኛ መሆናቸውን ገልጾ፤ ከዚህ ውስጥም 20 በመቶ ሚሆኑት (3.5 ሚሊዮን በላይ) መስማት የተሳናቸው ይላል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በ2013 ዓ.ም ባወጣው ቁጥራዊ ማስረጃ (Fact Sheet on Deafness and Hearing loss) ላይ ደግሞ በኢትዮጵያ ከ5 ሚሊዮን በላይ መስማት የመስማት ችግር ያለባቸው ዜጎች መኖራቸውን ይጠቅሳል።
ዩኒሴፍ ከሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር በ2008 ዓ.ም በሰራው ዳሰሳ የአካል ጉዳተኛ ዜጎች ከአጠቃላይ የህዝብ ቁጥሩ 9.3 በመቶ (7.8 ሚሊዮን) መሆኑን ያስቀምጣል፡፡ ከላይ በሁለቱም ጥናቶች የተወሰደውን ስሌት ተጠቅመን 20 በመቶዎቹ መስማት የተሳናቸው ናቸው ብንል ከ1.5 ሚሊዮን በላይ መስማት የተሳናቸው ዜጎች ይኖራሉ።
#ማስታወሻ፡ በተለያየ ጊዜያት የተሰሩትና ማግኘት የቻልናቸው የጥናት ውጤቶች ግኝት በጣም የተራራቁ ቢሆንም ለማሳያ ያክል የቀረቡ ናቸው። ቁጥራዊ መረጃዎቹ ወቅታዊ መረጃን ገላጭ አይደሉም፡፡ ተጨማሪ መረጃዎች ካሎት @RWethiopia ላይ ያካፍሉን
#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ
@tikvahethiopia
👍271❤39😱4🥰2😢2🤔1