TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሩስያ ያቀደችውን ታሳካለች " - ቭላድሚር ፑቲን የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከፈረንሳዩ አቻቸው ኢማኑኤል ማክሮን ጋር 90 ደቂቃ ያህል የፈጀ የስልክ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅት ፑቲን ሞስኮ ዩክሬን ውስጥ በምታካሂደው ዘመቻ ያቀደችውን ታሳካለች ብለዋል። ፑቲን አስተዳደራቸው የኪዬቭን ወታደራዊ እንቅስቃሴ በማስቆም ለሩሲያ ደኅንት ወታደራዊ ስጋት እንዳትሆን እናደርጋለን ስለማለታቸው…
" ከእኔ ጋር ቁጭ ብለህ ተነጋገር " - ቮልድሚር ዜኔንስኪ

የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቀጥታ ለመነጋገር ጠያቄ አቀረቡ።

ዜሌንስኪ ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ አመሻሽ ላይ በሰጡት መግለጫ ነው።

ፕሬዜዳንቱ ፤ " ጦርነቱን ለማቆም #ብቸኛው አማራጭ ከፑቲን ጋር በቀጥታ መነጋገር ነው " ብለዋል።

ዜሌንስኪ ለፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ፥ " ሩሲያን እያጠቃን አይደለም፤ ለማጥቃትም እቅዱ የለንም። ከእኛ ምንድነው የምትፈልገው ? መሬታችንን ትልቀቅ " ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ አክለው ፤ " ከእኔ ጋር ቁጭ ብለህ ተነጋገር። 30 ሜትር ሳይርቅ " በማለት ፑቲን ከፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ጋር በረዥሙ ጠረጴዛቸው ፊት ለፊት ያደረጉትን ንግግር አስታውስዋል።

ዜሌኒስኪ በመግለጫቸው ላይ #ምዕራባውያን ተዋጊ አውሮፕላኖችን እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።

" የአየር ክልሉን መዝጋት የማትችሉ ከሆነ ፤ አውሮፕላኖችን ስጡኝ " ሲሉ ነው ዜሌንስኪ የጠየቁት።

ምዕራባውያን የሩሲያ ተዋጊ አውሮፕላኖችን በዩክሬን ላይ ጥቃት እንዳያደርሱ የዩክሬንን አየር ክልል እንዲዘጉ ሲጠየቁ ቆይተዋል።

ዜሌንስኪ ፤ " በቀጣይ ሩሲያ ላትቪያ ፣ ሊትዌኒያ እና ኢስቶኒያን ልትወር ትችላለች " ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በሌላ መረጃ ፥ የሩስያ እና ዩክሬን ሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር ዛሬ በቤላሩስ ተጀምሯል።

@tikvahethiopia
👍1.16K👎109👏44😱30😢28🥰147