TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AxumUniversity

ማሕበረሰብ ኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ጉዕዞ ናብ ወፍሪ መኸተ ወራር ዕስለ አንበጣ!

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የአምበጣ መንጋ የመከላከል ዘመቻ ላይ ለመሳተፍ ጉዞ እያደረጉ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🙏1
#AxumUniversity

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የ2012 ተመራቂዎች የቲክቫህ አባላት እስካሁን አለመጠራታቸውን ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ እንደከተታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።

ተማሪዎቹ በትግራይ ክልል ያለውን ከባድ ሁኔታ ቢረዱም ለዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተሰጠው አይነት መፍትሄ በፍጥነት ተግባራዊ ይደረጋል ብለው ቢጠብቁም እስካሁን ምንም እንደሌለ ገልፀዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ጉዳይ የሚከታተለው የሀገር አቀፍ ተማሪዎች ህብረት የአስክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ጉዳይ ከዚህ በፊት ልክ እንደዓዲግራት መፍትሄ ያገኘ መሆኑን ገልጿል።

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ተመራቂ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጨርሰው በመውጣታቸው የዓዲግራት እንዲሁም የአክሱም ተማሪዎች መቐለ ገብተው ትምህርታቸውን እንዲጨርሱ በMoSHE አቅጣጫ ተቀምጧል።

በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል።

ለአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገም።

ተማሪዎችን ለመጥራት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በማስተባበር ላይ በመዘግየቱ ነው እስካሁን የቆየው።

ተመራቂ ተማሪዎችን ለመጥራት ስራዎች እየተሰሩ ፣ ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆኑን ተገልጿል።

በMoSHE አቅጣጫ መሰረት የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው የሚመረቁት መቐለ ዩኒቨርሲቲ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AxumUniversity

ለአክሱም ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጥሪ ተደረገ።

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎችን ጥር 20 እና 21 በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ኹሓ ካምፓስ ተቀብሎ እንደሚያስተምር አስታውቋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ገብረእየሱስ ብርሃነ የመማር ማስተማር ሂደትን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ለመግለጫ ሰጥተዋል።

ፕሮፌሰሩ ፥ ተማሪዎችም ሆኑ ወላጆች የደህንነት ስጋት ሳይገባቸው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ተመራቂዎቹ መገኘት እንዳለባቸው በመግለጽ ጥሪ አቅርበዋል።

በቀጣይም ሌሎች ተመራቂ ላልሆኑ ተማሪዎች ጥሪ በማድረግ ዩኒቨርሲቲው የሚያስተምር መሆኑንም ገልጸዋል። ~ ENA

@tikvahethiopia