#ቦረና
በኦሮሚያ ፣ ቦረና በድርቅ ሳቢያ በርካታ ወገኖቻችን ዛሬም ችግር ላይ ናቸው። እነዚህ ወገኖች በድርቁ ምክንያት ያላቸውን ከብቶች ስላጡ እጅግ በጣም ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ነው የሚኖሩት።
በድርቅ ተፈናቅለው መጠለያ ውስጥ ያሉ ወገኖች ሰሞኑን ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ሰጥተው የነበረ ሲሆን ያሉበት ሁኔታ እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው።
(በድብሉቅ ወረዳ የሚገኙ ተፈናቃዮች)
የ7 ልጆች እናት ወ/ሮ ጂሎ ጉራቻ ፦
" የዘንድሮው ድርቅ የነበሩንን ከብቶች እና ሁሉንም ንብረቶችን ነው ያወደመብን። ባዶ እጃችንን ስንሆን ወደዚህ መጣን ፤ እዚህ ከመጣን በኃላ በምግብ እና ውሃ እጥረት እየተቸገርን ነው። በተለይም ህፃናት ነፍሰጡር ሴቶች፣ አዛውንቶች በምግብ እጥረት እየተጎዱ ናቸው። እኛ እዚህ ከሰፈርን ከ6 ወር በላይ ሆኖናል። በመጠለያው በጣም ብዙ ቤተሰቦች ነው ያሉት። በቆይታችን አንዴ ብቻ ነው ለተወሰኑ ቤተሰቦች የምግብ ድጋፍ የተሰጠው እንጂ ምንም አላገኘንም። ስለዚህ በጣም ችግር ላይ ውስጥ ነው ያለነው። "
የ6 ልጆች አባት ዳለቻ ዲዳ ፦
" ምንጠጣው ውሃ በጣም የቆሸሸ ነው። እንስሳት ሲሞቱ ከሚጣሉበት ነው ልጆቻችን የሚቀዱልን። በዛ ላይ የመፀዳጃ ቦታም የለንም። እንዲሁ በበሩ ደጃፍ ነው ይህ ሁሉ በዚህ የሰፈረው ህዝብ የሚፀዳዳው ስለዚህ የበሽታ ወረርሽኝ ፍራቻ አለብን። ሌላው የመጠለያ ቦታና ላስቲክ ሰጥተውናል። ይህ ላስቲክ #ብርድ የሚከላከል አይደለም። እናም በጣም ችግር ውስጥ ነን። "
የልጆች እናቷ ትዬ አደንጌ ፦
" #ብርዱ_በጣም_አስቸጋሪ_ነው። ለምግብ ፍለጋ ነው ከእሳት አጠገብ የምንነሳው። በዛ ላይ የምንለብሰው ልብስ የለንም። በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው። "
ያንብቡ : https://telegra.ph/Borana-08-23 #ገልሞ_ዳዊት
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ፣ ቦረና በድርቅ ሳቢያ በርካታ ወገኖቻችን ዛሬም ችግር ላይ ናቸው። እነዚህ ወገኖች በድርቁ ምክንያት ያላቸውን ከብቶች ስላጡ እጅግ በጣም ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ነው የሚኖሩት።
በድርቅ ተፈናቅለው መጠለያ ውስጥ ያሉ ወገኖች ሰሞኑን ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ሰጥተው የነበረ ሲሆን ያሉበት ሁኔታ እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው።
(በድብሉቅ ወረዳ የሚገኙ ተፈናቃዮች)
የ7 ልጆች እናት ወ/ሮ ጂሎ ጉራቻ ፦
" የዘንድሮው ድርቅ የነበሩንን ከብቶች እና ሁሉንም ንብረቶችን ነው ያወደመብን። ባዶ እጃችንን ስንሆን ወደዚህ መጣን ፤ እዚህ ከመጣን በኃላ በምግብ እና ውሃ እጥረት እየተቸገርን ነው። በተለይም ህፃናት ነፍሰጡር ሴቶች፣ አዛውንቶች በምግብ እጥረት እየተጎዱ ናቸው። እኛ እዚህ ከሰፈርን ከ6 ወር በላይ ሆኖናል። በመጠለያው በጣም ብዙ ቤተሰቦች ነው ያሉት። በቆይታችን አንዴ ብቻ ነው ለተወሰኑ ቤተሰቦች የምግብ ድጋፍ የተሰጠው እንጂ ምንም አላገኘንም። ስለዚህ በጣም ችግር ላይ ውስጥ ነው ያለነው። "
የ6 ልጆች አባት ዳለቻ ዲዳ ፦
" ምንጠጣው ውሃ በጣም የቆሸሸ ነው። እንስሳት ሲሞቱ ከሚጣሉበት ነው ልጆቻችን የሚቀዱልን። በዛ ላይ የመፀዳጃ ቦታም የለንም። እንዲሁ በበሩ ደጃፍ ነው ይህ ሁሉ በዚህ የሰፈረው ህዝብ የሚፀዳዳው ስለዚህ የበሽታ ወረርሽኝ ፍራቻ አለብን። ሌላው የመጠለያ ቦታና ላስቲክ ሰጥተውናል። ይህ ላስቲክ #ብርድ የሚከላከል አይደለም። እናም በጣም ችግር ውስጥ ነን። "
የልጆች እናቷ ትዬ አደንጌ ፦
" #ብርዱ_በጣም_አስቸጋሪ_ነው። ለምግብ ፍለጋ ነው ከእሳት አጠገብ የምንነሳው። በዛ ላይ የምንለብሰው ልብስ የለንም። በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው። "
ያንብቡ : https://telegra.ph/Borana-08-23 #ገልሞ_ዳዊት
@tikvahethiopia
😢412👍164🙏42😱22❤14👎2🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ቦረና
በኦሮሚያ ክልል፤ ቦረና ዞን በተራዘመ ድርቅ በርካታ የቤት እንስሳት አልቀው የሚላስ የሚቀመስ ያጡ ነዋሪዎችም ከድርቁ ጋር በተያያዘ መሞት መጀመራቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ቦረና ዞን የተራዘመው ድርቅ የአርሶ አደሮችን በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶቻቸውን በመግደል አስከፊነቱን የቀጠለ ሲሆን የሰዎችም ህይወት በድርቁ ሳቢያ እያለፈ ነው ተብሏል።
በቦረና ዞን ተልተሌ ወረዳ ነዋሪው አርብቶ አደር ማሊቻ ሞሌ ከድርቁ ጋር በተያያዘ ሰዎች እየሞቱ ስለመሆኑ ለሬድዮ ጣቢያው እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል ፦
" ... በድርቁ ሰው የከፋ ችግር ውስጥ ነው ያለው ። ያላቸው ከብቶች በግ እና ፍየል እንኳ ሳይቀር አልቀዋል። ጠብ ያለ ዝናብ ባለመኖሩ የሚወጣ እህል የለም።
የሚሸጥ ከብት በሙሉ በድርቁ አልቀዋል። አሁን ሰው በችግሩ በሕይወት እስከማለፍ ደርሷል። የሚቀመስ በመጥፋቱ በዚሁ ዓመት ብቻ በዚህች ቀበሌያችን አራት ሰው የሚደርስ ተጎሳቅለው አልፈዋል ። "
በደቡብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍሎች ድርቁ የከፋ መሆኑን ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል፤ ቦረና ዞን በተራዘመ ድርቅ በርካታ የቤት እንስሳት አልቀው የሚላስ የሚቀመስ ያጡ ነዋሪዎችም ከድርቁ ጋር በተያያዘ መሞት መጀመራቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ቦረና ዞን የተራዘመው ድርቅ የአርሶ አደሮችን በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶቻቸውን በመግደል አስከፊነቱን የቀጠለ ሲሆን የሰዎችም ህይወት በድርቁ ሳቢያ እያለፈ ነው ተብሏል።
በቦረና ዞን ተልተሌ ወረዳ ነዋሪው አርብቶ አደር ማሊቻ ሞሌ ከድርቁ ጋር በተያያዘ ሰዎች እየሞቱ ስለመሆኑ ለሬድዮ ጣቢያው እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል ፦
" ... በድርቁ ሰው የከፋ ችግር ውስጥ ነው ያለው ። ያላቸው ከብቶች በግ እና ፍየል እንኳ ሳይቀር አልቀዋል። ጠብ ያለ ዝናብ ባለመኖሩ የሚወጣ እህል የለም።
የሚሸጥ ከብት በሙሉ በድርቁ አልቀዋል። አሁን ሰው በችግሩ በሕይወት እስከማለፍ ደርሷል። የሚቀመስ በመጥፋቱ በዚሁ ዓመት ብቻ በዚህች ቀበሌያችን አራት ሰው የሚደርስ ተጎሳቅለው አልፈዋል ። "
በደቡብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍሎች ድርቁ የከፋ መሆኑን ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
😢1.54K👍355🙏27🕊26❤13👎11😱8🤔4🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቦረና በኦሮሚያ ክልል፤ ቦረና ዞን በተራዘመ ድርቅ በርካታ የቤት እንስሳት አልቀው የሚላስ የሚቀመስ ያጡ ነዋሪዎችም ከድርቁ ጋር በተያያዘ መሞት መጀመራቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል። ቦረና ዞን የተራዘመው ድርቅ የአርሶ አደሮችን በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶቻቸውን በመግደል አስከፊነቱን የቀጠለ ሲሆን የሰዎችም ህይወት በድርቁ ሳቢያ እያለፈ ነው ተብሏል። በቦረና…
#ቦረና
- በቦረና ዞን ካሉት የቀንድ ከብቶች ውስጥ 10 በመቶውን ለመታደግ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ያስፈልጋል።
- በድርቁ ምክንያት በዞኑ ከ3 ሚሊየን በላይ እንስሳት የሞቱ ሲሆን ፥ ከዚህ ውስጥ 85 በመቶዎቹ የቀንድ ከብቶች ናቸው።
- በዞኑ የቀሩት 230 ሺህ የቀንድ ከብቶች ሲሆኑ፤ ለ3 ወር የቀንድ ከብቶቹን ለመታደግ ቢያንስ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ማቅረብ ያስፈልጋል። በተጨማሪ 135 ሺህ ኩንታል መኖ የሚያስፈልግ ሲሆን በዞኑ ማቅረብ የተቻለው አንድ በመቶ ብቻ ነው።
- እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ የታሰበውን ያህል ችግር ውስጥ የሚገኙ ከብቶችን መታደግ ከባድ ሊሆን ይችላል።
- እስካሁን በቀንድ ከብቶች ሞት ምክንያት 33 ቢሊየን የሚገመት ብር ታጥቷል።
(የቦረና ዞን አስተዳደሪ ጃርሶ ቦሩ ለኤፍ ቢ ሲ ከሰጡት ቃል)
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
- በቦረና ዞን ካሉት የቀንድ ከብቶች ውስጥ 10 በመቶውን ለመታደግ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ያስፈልጋል።
- በድርቁ ምክንያት በዞኑ ከ3 ሚሊየን በላይ እንስሳት የሞቱ ሲሆን ፥ ከዚህ ውስጥ 85 በመቶዎቹ የቀንድ ከብቶች ናቸው።
- በዞኑ የቀሩት 230 ሺህ የቀንድ ከብቶች ሲሆኑ፤ ለ3 ወር የቀንድ ከብቶቹን ለመታደግ ቢያንስ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ማቅረብ ያስፈልጋል። በተጨማሪ 135 ሺህ ኩንታል መኖ የሚያስፈልግ ሲሆን በዞኑ ማቅረብ የተቻለው አንድ በመቶ ብቻ ነው።
- እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ የታሰበውን ያህል ችግር ውስጥ የሚገኙ ከብቶችን መታደግ ከባድ ሊሆን ይችላል።
- እስካሁን በቀንድ ከብቶች ሞት ምክንያት 33 ቢሊየን የሚገመት ብር ታጥቷል።
(የቦረና ዞን አስተዳደሪ ጃርሶ ቦሩ ለኤፍ ቢ ሲ ከሰጡት ቃል)
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
😢1.24K👍334🙏28👎23🕊21😱20❤9🤔9🥰7
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቦረና - በቦረና ዞን ካሉት የቀንድ ከብቶች ውስጥ 10 በመቶውን ለመታደግ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ያስፈልጋል። - በድርቁ ምክንያት በዞኑ ከ3 ሚሊየን በላይ እንስሳት የሞቱ ሲሆን ፥ ከዚህ ውስጥ 85 በመቶዎቹ የቀንድ ከብቶች ናቸው። - በዞኑ የቀሩት 230 ሺህ የቀንድ ከብቶች ሲሆኑ፤ ለ3 ወር የቀንድ ከብቶቹን ለመታደግ ቢያንስ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ማቅረብ ያስፈልጋል። በተጨማሪ…
#ቦረና
የቡሳ ጎኖፋ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ማሊቻ ሎጄ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሰጡት ቃል ፦
- ቦረና ዞን በተፈጠረው ድርቅ ምክንያት የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቶ ቁጥሩ ከ604 ሺህ በላይ ደርሷል።
- ድርቁ በቦረና ብቻ ሳይሆን ሁለቱን የጉጂ ዞኖች ጨምሮ በ10 ዞኖች የተከሰተ ነው። ቦረና ግን ቆላማነቱ ከሌሎቹ አካባቢዎች ከፍተኛ በመሆኑ የጉዳቱ መጠንም በዚያው መጠን ሊጨምር ችሏል።
- በሁለት ወቅቶች (የካቲት እና ሰኔ) የድርቁ ሁኔታ ያለበትን ለማወቅ ጥናት ይካሄዳል በዚሁ መሠረት ዘንድሮም ድርቁ መቀጠሉ ስለተረጋገጠ ክልሉ ዕቅዶችን አውጥቶ በየደረጃው እየተንቀሳቀሰ ነው።
- ለድርቁ ምላሽ ለመስጠት ለተጋላጮችም እገዛ ለማድረግ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም ካለው የችግር ስፋት አኳያ የሚፈለገውን እርዳታ ማድረግ አልተቻለም።
- አስቸኳይ የመድኃኒት አቅርቦት፣ የእናቶች እና ሕፃናት አልሚ ምግቦች እና ሌሎች ሕይወት አድን ድጋፎች ስለሚያስፈልጉ ሁሉም አካላት በትብብር ሊሠሩ ይገባል።
ያንብቡ ; https://telegra.ph/EBC-02-23
@tikvahethiopia
የቡሳ ጎኖፋ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ማሊቻ ሎጄ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሰጡት ቃል ፦
- ቦረና ዞን በተፈጠረው ድርቅ ምክንያት የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቶ ቁጥሩ ከ604 ሺህ በላይ ደርሷል።
- ድርቁ በቦረና ብቻ ሳይሆን ሁለቱን የጉጂ ዞኖች ጨምሮ በ10 ዞኖች የተከሰተ ነው። ቦረና ግን ቆላማነቱ ከሌሎቹ አካባቢዎች ከፍተኛ በመሆኑ የጉዳቱ መጠንም በዚያው መጠን ሊጨምር ችሏል።
- በሁለት ወቅቶች (የካቲት እና ሰኔ) የድርቁ ሁኔታ ያለበትን ለማወቅ ጥናት ይካሄዳል በዚሁ መሠረት ዘንድሮም ድርቁ መቀጠሉ ስለተረጋገጠ ክልሉ ዕቅዶችን አውጥቶ በየደረጃው እየተንቀሳቀሰ ነው።
- ለድርቁ ምላሽ ለመስጠት ለተጋላጮችም እገዛ ለማድረግ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም ካለው የችግር ስፋት አኳያ የሚፈለገውን እርዳታ ማድረግ አልተቻለም።
- አስቸኳይ የመድኃኒት አቅርቦት፣ የእናቶች እና ሕፃናት አልሚ ምግቦች እና ሌሎች ሕይወት አድን ድጋፎች ስለሚያስፈልጉ ሁሉም አካላት በትብብር ሊሠሩ ይገባል።
ያንብቡ ; https://telegra.ph/EBC-02-23
@tikvahethiopia
😢570👍252👎23🙏7😱6❤4🥰4🕊4