TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢትዮ. አየር መንገድ ከግጭት ተረፈ⬇️

ዘ ኢስት አፍሪካን እንደዘገበው ባለፈው #ረቡዕ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ኢት 858፣ ቦይንግ 737-800 ከጣሊያኑ የሌዢር ኤርላይን ኒዮስ ቦይንግ 767-306 R የበረራ ቁጥር NOS 252 ጋር በኬንያ ሰማይ ላይ #ለመጋጨት ሲቃረብ #በአንድ ደቂቃ ልዩነት ተርፏል።

አደጋ ተፈጥሮ ቢሆን ኖሮ በአለም አሰቃቂው የአውሮፕላን አደጋ ተብሎ ይመዘገብ እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል። ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ በ37 ሺ ጫማ ከፍታ ላይ በመብረር ላይ የነበረ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ቀን ምሽት 12 ሰዓት ላይ የጣሊያን አውሮፕላን ከቪሮና ተነስቶ ወደ ዛንዚባር በማምራት ላይ ነበር። እኩለ ሌሊት ላይ ሁለቱም አውሮፕላኖች ወደ ኬንያ አየር ክልል የገቡ ሲሆን፣ ሁለቱም ለግጭት በሚያደርሳቸው ሁኔታ ፊት ለፊት እየተጓዙ እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል።

የግጭት መቆጣጠሪያ መሳሪያው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስጠንቀቂያ መልዕክት እንዳስተላለፈ ፣ ፓይለቱ በአንድ ደቂቃ ውስጥ ወደ 38 ሺ ጫማ ከፍ በማድረግ እና ለ5 ደቂቃ በዚሁ ከፍታ ላይ በመቆየት አደጋ እንዳይፈጠር ለማድረግ ችሎአል። የኬንያ አየር ተቆጣጣሪዎች የኢትዮጵያን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ተጠያቂ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ የአየር ታረፊክ ተቆጣጣሪዎች
እንደገለጹት የጣሊያን አየር መንገድ አስቀድሞ በምን ያክል ከፍታ እንደሚበር ሲገልጽ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን ይህን ባለማድረጉ አደጋው ሊደርስ እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አደጋው ከመድረሱ አራት ቀናት በፊት የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር።

ይህንን ተከትሎ የኬንያ አየር መንገድ ከ አዲስ አበባ የሚነሱና ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ በረራዎች ደህንነታቸው አስተማማኝ አለመሆኑን አስቀድሞ #ማስጠንቀቂያ ልኮ እንደነበር ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን በኬንያ በኩል የቀረበውን ክስ ውድቅ አድርጎታል። የኬንያ አየር ተቆጣጣሪ ያወጣው መግለጫ ሃሰትና መሰረተ ቢስ ነው ያለው የሲቪል አቬሽን ባለስልጣን፣ እንዲህ አይነት አደጋ ይከሰታል የሚል መረጃ ለኢትዮጵያአየር ተቆጣጣሪዎች አለመነገሩን ገልጿል።

📌የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን ለአድማ አነሳስተዋል የተባሉ 9 አመራሮችና ሰራተኞች #መታሰራቸው ይታወቃል።

©ESAT
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🙏1
ብርጋዴር ጀኔራል #አሳምነው_ጽጌ

"በቅማንት ስም የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች በሰነዘሩት ጥቃት #በአንድ መንደር 200 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ 2 ሺ ዜጎች ተፈናቅለዋል፤ 55 ሰዎች ሞተዋል፡፡"
.
.

"ከሌላ አካባቢ መጥተው #በግጭት ሲሳተፉ የነበሩና የሞቱ ሶስት ሰዎች መኖራቸውን መታወቂያቸውን በመመልከት #አረጋግጠናል፡፡"
.
.

"ጥፋት #ለመፈጸም የተደራጀው ኃይል ለጊዜው #ተገቷል፤ የታጠቁ ኃይሎች በመሸጉበት ስፍራ ተደምስሰዋል፡፡ በአማራ ክልል በኦሮሚያ ልዩ ዞን ባቲ አካባቢና በጎረቤት ክልልም ሕገወጥ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች በቅርብ ርቀት አሉ። የእኛን እርምጃ ወስደናል፡፡ የቀረውንም ከሚመለከታቸው ጋር #መፍትሄ ለመስጠት በቅንጅት እየሰራን ነው፡፡"

©አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ ማጠናቀቁ ተገልጿል።

ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን ሶስተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ በማሳደግ ነው ስራውን ሰርቶ ያጠናቀቀው።

ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ የተለያዩ ግብዓቶች ሲጓጓዙ በመንገድ ላይ እስከ ሁለት ሳምንት ይቆዩ የነበረ ሲሆን በተከናወነው መንገድ የማሻሻል ጥገና ስራ የግድቡ የግንባታ ግብዓቶች #በአንድ_ቀን ለመድረስ ይችላሉ ተብሏል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት

@tikvahethiopia
👍8👎2