#Ethiopia
የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልኡክ ጄፈሪ ፊልትማን ጋር መወያየታቸውን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ይፋ ባደረገው መረጃ ፤ በውይይቱ ወቅት ከአሸባሪው ሕወሐት ጋር የሚደረገው ጦርነት ስለሚቆምበት መንገድ የአሜሪካ ሐሳብ ምን እንደሆነ በልዩ ልኡኩ በኩል የተነሣ ሲሆን፣ አቶ ደመቀ የኢትዮጵያን አቋም አስረድተዋል።
አቶ ደመቀ መኮንን #በኮምቦልቻ እና #በላሊበላ ለሰብአዊ ርዳታ የሚውሉ በረራዎች መፈቀዳቸውን የገለፁ ሲሆን ወደ ትግራይም 369 ርዳታ የጫኑ መኪናዎች እንዲገቡ መፈቀዱን ገልፀዋል።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎችን ሁኔታ በተመለከተም ውይይት አድርገዋል።
አቶ ደመቀ ፥ " አሸባሪው ሕወሐት አሁንም ቢሆን በአፋርና በአማራ ክልሎች ጥቃት እየፈጸመና ከፍተኛ ሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድመት እንዲሁም ሥነ ልቡናዊ ጉዳት እያደረሰ ነው " ያሉ ሲሆን ህወሓት ከሁለቱ ክልሎች ለቅቆ እንዲወጣ ግፊት ሊደረግበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልኡክ ጄፈሪ ፊልትማን ጋር መወያየታቸውን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ይፋ ባደረገው መረጃ ፤ በውይይቱ ወቅት ከአሸባሪው ሕወሐት ጋር የሚደረገው ጦርነት ስለሚቆምበት መንገድ የአሜሪካ ሐሳብ ምን እንደሆነ በልዩ ልኡኩ በኩል የተነሣ ሲሆን፣ አቶ ደመቀ የኢትዮጵያን አቋም አስረድተዋል።
አቶ ደመቀ መኮንን #በኮምቦልቻ እና #በላሊበላ ለሰብአዊ ርዳታ የሚውሉ በረራዎች መፈቀዳቸውን የገለፁ ሲሆን ወደ ትግራይም 369 ርዳታ የጫኑ መኪናዎች እንዲገቡ መፈቀዱን ገልፀዋል።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎችን ሁኔታ በተመለከተም ውይይት አድርገዋል።
አቶ ደመቀ ፥ " አሸባሪው ሕወሐት አሁንም ቢሆን በአፋርና በአማራ ክልሎች ጥቃት እየፈጸመና ከፍተኛ ሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድመት እንዲሁም ሥነ ልቡናዊ ጉዳት እያደረሰ ነው " ያሉ ሲሆን ህወሓት ከሁለቱ ክልሎች ለቅቆ እንዲወጣ ግፊት ሊደረግበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
👍1