#ትኩረት
ከማለዳው አንስቶ በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ጃርዴጋ ጃርቴ ወረዳ የፀጥታ ችግር መኖሩንና ንፁሃን ሰዎች ላይ በታጣቂዎች ጥቃት መከፈቱን ነዋሪዎች እየገለፁ ይገኛሉ።
እስካሁን ባለው ሁኔታ በቁጥር ያልተለዩ ሰዎች ህይወት መጥፋቱን የገለፁት ነዋሪዎች አካባቢው አሁንም ባለመረጋጋቱ ተጨማሪ ጥፋት ስለሚደርስ የመንግስት የፀጥታ ኃይል ወደ ስፍራው ገብቶ እንዲያረጋጋ ተማፅነዋል።
በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው የጦርነት ሁኔታ በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ያለውን ህዝብ ደህንነት እንዲዘነጋ ማድረጉን ፤ ሚዲያዎችም ችላ እንዲሉት እያደረገ መሆኑን በአካባቢው ቤተሰቦቻቸው ያሉ አባላት ገልፀዋል።
@tikvahethiopia @OfficialtikvahethiopiaBoT
ከማለዳው አንስቶ በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ጃርዴጋ ጃርቴ ወረዳ የፀጥታ ችግር መኖሩንና ንፁሃን ሰዎች ላይ በታጣቂዎች ጥቃት መከፈቱን ነዋሪዎች እየገለፁ ይገኛሉ።
እስካሁን ባለው ሁኔታ በቁጥር ያልተለዩ ሰዎች ህይወት መጥፋቱን የገለፁት ነዋሪዎች አካባቢው አሁንም ባለመረጋጋቱ ተጨማሪ ጥፋት ስለሚደርስ የመንግስት የፀጥታ ኃይል ወደ ስፍራው ገብቶ እንዲያረጋጋ ተማፅነዋል።
በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው የጦርነት ሁኔታ በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ያለውን ህዝብ ደህንነት እንዲዘነጋ ማድረጉን ፤ ሚዲያዎችም ችላ እንዲሉት እያደረገ መሆኑን በአካባቢው ቤተሰቦቻቸው ያሉ አባላት ገልፀዋል።
@tikvahethiopia @OfficialtikvahethiopiaBoT
😢640👍299🕊45🙏36😱28❤18
#ትኩረት
የመተሐራ ቲክቫህ ቤተሰቦች በሚኖሩበት የመተሀራ አካባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ በላኳቸው መልዕክቶች አስገንዝበዋል።
ከዚህ ቀደም ወደ መተሀራ አካባቢ በርካታ ወጣቶች በመዝናኛ ቦታ እያሉ መገደላቸው በሚዲያዎችም ጭምር መገለፁ ይታወሳል።
እዛው " መተሐራ " አካባቢ ከአምስት ቀናቶች በፊት አንድ የቀበሌ ሊቀመንበር ተገድሎ ነበር ፤ ከዚህ ግድያ በኃላም የአካባቢው ነዋሪዎች የሆኑ ሰዎች መገደላቸውን የመተሐራ ቤተሰቦቻችን ገልፀዋል።
ከሚፈፀሙ ግድያዎች በተጨማሪ ደግሞ ታጣቂዎች ሰዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ (እስከ 2 ሚሊዮን ብር) ድረስ የመጠየቅ እንቅስቃሴ እየተበራከተ በመሆኑ ጉዳዩ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እየደረሰ ነውና ከመቼውም በላይ ልዩ ትኩረት ይፈጋል ሲሉ አስገዝበዋል።
በተጨማሪ ከአዳማ ከ50 እስከ 100 ኪ/ሜ ባለው ርቀት ውስጥ ባሉት አቦምሳ / አፐር አዋሽ አካባቢም ትኩረትን እንደሚሻ አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል ፤ አንድ የቅርብ ቤተሰቡ በታጣቂዎች የተገደሉበት የቤተሰባችን አባልም በተመሳሳይ መልዕክት በመላክ የአካባቢው ደህንነት ልዩ ትኩረት እንደሚሻ አስገንዝቧል።
ከአዳማ ወደ መተሀራ በሚወስደው መንገድ ላይ " ኑራሄራ " አካባቢ የሰዎች ግድያ እና እገታ እንዳለ የገለፀው ቤተሰባችን ከቀናት በፊት ዘመዱ መገደሉን አመልክቷል።
" የእናቴ አጎት ነው ለባለቤቱ ደውለው መጀመሪያ ብር አምጪ ነው የተባለችው። ብር ማምጣት አንችልም አለች ፤ ከዘመድም ቢሆን ጠይቂና አምጪ አሏት ፤ ብር ሊሰጥ የሚችል ዘመድ የለም የራሳችሁን የምትወስኑትን ውሳኔ ወስኑ ስትል ነው የመቱት " ሲል አስረድቷል።
" እኔም ለለቅሶ ወደዛ ሄጄ ነበር " ያለው ቤተሰባችን በአካባቢው የሚሰማው ሁሉ የደህንነት ስሜትን የሚነሳ ነው እና በተለይ ፌዴራል መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የአካባቢውን ድህንነት ማረጋገጥና አጥፊዎችን መቆጣጠር አለበት ሲል አጥብቆ አስገንዝቧል።
በተጨማሪም ይኸው ቤተሰባችን በቦሌ ወደ አዳማ በሶደሬ በኩል በሚወስደው መንገድ ቦፋ እና አውራ ጎዳና በሚባለው ቦታ የህዝብ ተሽከርካሪ ሳይቀር የማገት ድርጊት ተፈፅሞም እንደነበር በመጠቆም አጠቃላይ ለደህንነት ስጋት በሆኑ ቦታዎች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ መንግስት የተጠናከረ ስራ እንዲሰራ መልዕክቱን አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
የመተሐራ ቲክቫህ ቤተሰቦች በሚኖሩበት የመተሀራ አካባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ በላኳቸው መልዕክቶች አስገንዝበዋል።
ከዚህ ቀደም ወደ መተሀራ አካባቢ በርካታ ወጣቶች በመዝናኛ ቦታ እያሉ መገደላቸው በሚዲያዎችም ጭምር መገለፁ ይታወሳል።
እዛው " መተሐራ " አካባቢ ከአምስት ቀናቶች በፊት አንድ የቀበሌ ሊቀመንበር ተገድሎ ነበር ፤ ከዚህ ግድያ በኃላም የአካባቢው ነዋሪዎች የሆኑ ሰዎች መገደላቸውን የመተሐራ ቤተሰቦቻችን ገልፀዋል።
ከሚፈፀሙ ግድያዎች በተጨማሪ ደግሞ ታጣቂዎች ሰዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ (እስከ 2 ሚሊዮን ብር) ድረስ የመጠየቅ እንቅስቃሴ እየተበራከተ በመሆኑ ጉዳዩ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እየደረሰ ነውና ከመቼውም በላይ ልዩ ትኩረት ይፈጋል ሲሉ አስገዝበዋል።
በተጨማሪ ከአዳማ ከ50 እስከ 100 ኪ/ሜ ባለው ርቀት ውስጥ ባሉት አቦምሳ / አፐር አዋሽ አካባቢም ትኩረትን እንደሚሻ አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል ፤ አንድ የቅርብ ቤተሰቡ በታጣቂዎች የተገደሉበት የቤተሰባችን አባልም በተመሳሳይ መልዕክት በመላክ የአካባቢው ደህንነት ልዩ ትኩረት እንደሚሻ አስገንዝቧል።
ከአዳማ ወደ መተሀራ በሚወስደው መንገድ ላይ " ኑራሄራ " አካባቢ የሰዎች ግድያ እና እገታ እንዳለ የገለፀው ቤተሰባችን ከቀናት በፊት ዘመዱ መገደሉን አመልክቷል።
" የእናቴ አጎት ነው ለባለቤቱ ደውለው መጀመሪያ ብር አምጪ ነው የተባለችው። ብር ማምጣት አንችልም አለች ፤ ከዘመድም ቢሆን ጠይቂና አምጪ አሏት ፤ ብር ሊሰጥ የሚችል ዘመድ የለም የራሳችሁን የምትወስኑትን ውሳኔ ወስኑ ስትል ነው የመቱት " ሲል አስረድቷል።
" እኔም ለለቅሶ ወደዛ ሄጄ ነበር " ያለው ቤተሰባችን በአካባቢው የሚሰማው ሁሉ የደህንነት ስሜትን የሚነሳ ነው እና በተለይ ፌዴራል መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የአካባቢውን ድህንነት ማረጋገጥና አጥፊዎችን መቆጣጠር አለበት ሲል አጥብቆ አስገንዝቧል።
በተጨማሪም ይኸው ቤተሰባችን በቦሌ ወደ አዳማ በሶደሬ በኩል በሚወስደው መንገድ ቦፋ እና አውራ ጎዳና በሚባለው ቦታ የህዝብ ተሽከርካሪ ሳይቀር የማገት ድርጊት ተፈፅሞም እንደነበር በመጠቆም አጠቃላይ ለደህንነት ስጋት በሆኑ ቦታዎች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ መንግስት የተጠናከረ ስራ እንዲሰራ መልዕክቱን አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
👍740😢146🕊45🙏20👎13😱11❤1