TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AmharaPolice

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን " በተለያዩ ወንጀሎች ጠርጥሬ ስፈልገው የነበረው ዘመነ ካሴን በቁጥጥር ስር አውያለሁ " ሲል ዛሬ አሳውቋል።

የአማራ ፖሊስ ዘመንን በባህር ዳር ቀበሌ 3 በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ተደብቆ በህብረተሰቡ ጥቆማ እንደያዘው ገልጿል።

" በወቅቱ ከ500 ሺህ ብር በላይ በኢግዚቢት የተያያዘ ሲሆን ቀሪ የምርመራና የፍተሻ ሂደቶች እየተከወኑ ነው " ሲል የአማራ ፖሊስ አመልክቷል።

የአማራ ፖሊስ ምርመራው የሚካሄደው #በክልሉ ፖሊስ መሆኑንም አሳውቋል።

ዘመነ ካሴ በቀድሞ የአርበኞች ግንቦት 7 ውስጥ በአባልነትና በአመራር ውስጥ የነበረ እና ረጅም ጊዜ በኤርትራ በርሀ ውስጥ በመሆን ኢህአዴግ መራሹን አገግዛ ሲታገል ያሳለፈ ፤ በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎም ውጭ ያሉ የታጠቁ አካላት ትጥቃቸው አውርደው ወደ ሀገር ሲገቡ ወደ ሀገር የገባ ሲሆን ወደ ሀገር ከገባ በኃላ በፋኖ አደረጃጀት እንቅስቃሴ ውስጥ በፊት መስመር ላይ ከሚታወቁት ግለሰቦች መካከል አንዱ ነው።

በአማራ ክልል በጎጃም አካባቢ የሚንቀሳቀውና እራሱን " የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ " በማለት የሚጠራው ቡድን ሰብሳቢ እንደሆነም ዘመነ ካሴ ከዚህ ቀደም ለአንድ የውጭ ሚዲያ ተናግሮ ነበር።

@tikvahethiopia
👎2.5K👍1.21K😢114😱7453🙏42🕊9