TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#KFO #AWADAY #OFC

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን አወዳይ ከተማ ላይ ተፈጽሟል ያለውን ኢ ሰብዓዊ ድርጊት የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አጣርቶ ውሳኔ እንዲያስተላልፍበት ኦፌኮ ጠይቋል።

የኦፌኮ ለፓርላማው በጻፈው የአቤቱታ ደብዳቤው የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም ለማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨውና ዜጎች እየተቀባበሉ ስለተመለከቱት በአወዳይ ከተማ ማህበረሰብ ላይ የመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች ሲፈጽሙት የሚታየውን ጭካኔ የተሞላበት ደብደባና ግድያ ጉዳይ እንዲጣራ ነው የጠየቀው፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረው የድምጽ ምስል መረጃ በቀላሉ የምንመለከተው አይደለም ያለው ኦፌኮ ድርጊቱም እጅግ አሳዝኖኛል ብሏል፡፡

ከዚህ ቀደም ሐምሌ 30/2008 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የፀጥታ ሀይሎች በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ ሲፈጽሙ ከሚታየው ኢ ሰብዓዊ ድርጊት ጋር ተመሳሳይ መሆኑን የጠቀሰው ኦፌኮ ም/ቤቱ እንዲህ አይነት ድርጊቶችን አጣርቶ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል፡፡

በአወዳይ ከተማ ተፈጽሟል የተባለውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትም ፓርላማ አስቸኳይ ምርመራ አድርጎ እንዲወያይበትና ውሳኔ እንዲሰጥበት ኦፌኮ ጠይቋል፡፡

ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia