ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል‼️
ባለፈው ሳምንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ያሶ ከተማ በፈፀመ ጥቃት #ስምንት የአንድ ቤተሰብ አባላት #መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች ለቢቢሲ ተናገሩ።
ህዳር 11 ቀን 2011 ማታ ከሶስት ሰዓት በኋላ ታጣቂዎች የቤተሰብ አባላቱን በጥይት ገድለው ቤታቸውንም እንዳቃጠሉ በጥቃቱ ባለቤታቸውንና የባለቤታቸውን ወንድሞች ያጡት የስምንት ልጆች እናት ወ/ሮ #ልኪቱ_ተፈራ ይናገራሉ።
"መጀመሪያ ተኩስ ከከፈቱብን በኋላ ቤት ውስጥ ጭድ ጨምረው እሳት ለኮሱብን። እኔና ልጆቼ በጓሮ በር በኩል አመለጥን። ሌሎቹ ግን እዚያው ተቃጠሉ" በማለት ሁኔታውን ያስታውሳሉ።
ልጃቸው አቶ ወጋሪ ፈይሳ በመኖሪያ ቤታቸው በወቅቱ ሃያ አንድ የቤተሰብ አባላት እንደነበሩና ቤታቸውም ፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ በመሆኑ ደህንነት ተሰምቷቸው እንደነበር ይናገራል።
ነገር ግን ያልጠበቁት ነገር መከሰቱንና በተፈጠረው ነገርም ህፃናት ልጆች ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ እንዳሉም ይገልፃሉ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙሳ አህመድ ከተማው ውስጥ ግድያ ስለ መከሰቱ መረጃ እንዳላቸው ነገር ግን ዝርዝር ጉዳዮችን እንደማያውቁ ገልፀዋል።
ከጥቃቱ የተረፉ የቤተሰቡ አባላት ሸሽተው የተጠለሉበት አዋሳኝ የምሥራቅ ወለጋ ሃሮ ሊሙ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጋሮማ ቶሎሳ ግድያው ስለመፈፀሙ ማረጋገጫ እንዳላቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።
"አባቴ ፈይሳ ዲሳሳ፣ ወንድሙ ዲንሳ ዲሳሳን ጨምሮ ስምንት የአጎቶቼ ልጆችን አጥተናል። ግድያው በጣም አሰቃቂ ነበር" ይላሉ አቶ ዋጋሪ።
በተመሳሳይ እለት የቤተሰብ አባላቱን ግድያ ጨምሮ በያሶ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት አርባ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ኗሪዎችና የአዋሳኝ ወረዳ አስተዳዳሪው ቢናገሩም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊው አቶ ሙሳ ግን አስር ሰው ብቻ ስለመገደሉ መረጃ እንዳላቸው ይገልፃሉ።
ሆኖም ግን ጉዳዩን በሚመለከት ተጨማሪ መረጃ እንደሚያስፈልጋቸው "መንገድ በመዘጋቱ ነገሮችን በቅርበት ማጣራት አልቻልንም" በማለት ተናግረዋል።
አቶ ሙሳ እንደሚሉት የረቡዕ ጥቃት ከመፈፀሙ ከጥቂት ቀናት በፊት ሁለት የመንግሥት ሰራተኞች ተገድለዋል። አርብ እለትም ደግሞ በካማሼ ሌሎች ሦስት ሰዎች መሞታቸውንም ገልፀዋል።
በያሶ ጥቃቱን የፈፀሙት ታጣቂዎች ከመሆናቸው በዘለለ ስለታጣቂዎቹ እስካሁን ምንም የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለ አቶ ሙሳ ይናገራሉ።
'ያፈነገጡ የኦነግ ታጣቂዎች' ለአካባቢው ስጋት እየሆኑ እንደሆነ አቶ ሙሳ ቢናገሩም ያነጋገርናቸው ኗሪዎች እና የአዋሳኝ ወረዳ ሃላፊዎች ግን በአካባቢው #የኦነግ ታጣቂ እንደሌለ ገልፀዋል።
በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ አራት የካማሺ ዞን ሃላፊዎች አሶሳ ከተማ ስብሰባ ቆይተው ወደ ካማሺ በመመለስ ላይ ሳሉ በተከፈተባቸው ተኩስ ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ብዙዎች መገደላቸውንና ወደ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ከቀያቸው መፈናቀላቸው ይታወሳል።
በአሁኑ ወቅት ግን ነገሮችን #ለመቆጣጠር በያሶ ከተማ ፌደራል ፖሊስ፤ በካማሽ ደግሞ መከላከያ ሠራዊት እንደገባ አቶ ሙሳ ገልፀዋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባለፈው ሳምንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ያሶ ከተማ በፈፀመ ጥቃት #ስምንት የአንድ ቤተሰብ አባላት #መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች ለቢቢሲ ተናገሩ።
ህዳር 11 ቀን 2011 ማታ ከሶስት ሰዓት በኋላ ታጣቂዎች የቤተሰብ አባላቱን በጥይት ገድለው ቤታቸውንም እንዳቃጠሉ በጥቃቱ ባለቤታቸውንና የባለቤታቸውን ወንድሞች ያጡት የስምንት ልጆች እናት ወ/ሮ #ልኪቱ_ተፈራ ይናገራሉ።
"መጀመሪያ ተኩስ ከከፈቱብን በኋላ ቤት ውስጥ ጭድ ጨምረው እሳት ለኮሱብን። እኔና ልጆቼ በጓሮ በር በኩል አመለጥን። ሌሎቹ ግን እዚያው ተቃጠሉ" በማለት ሁኔታውን ያስታውሳሉ።
ልጃቸው አቶ ወጋሪ ፈይሳ በመኖሪያ ቤታቸው በወቅቱ ሃያ አንድ የቤተሰብ አባላት እንደነበሩና ቤታቸውም ፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ በመሆኑ ደህንነት ተሰምቷቸው እንደነበር ይናገራል።
ነገር ግን ያልጠበቁት ነገር መከሰቱንና በተፈጠረው ነገርም ህፃናት ልጆች ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ እንዳሉም ይገልፃሉ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙሳ አህመድ ከተማው ውስጥ ግድያ ስለ መከሰቱ መረጃ እንዳላቸው ነገር ግን ዝርዝር ጉዳዮችን እንደማያውቁ ገልፀዋል።
ከጥቃቱ የተረፉ የቤተሰቡ አባላት ሸሽተው የተጠለሉበት አዋሳኝ የምሥራቅ ወለጋ ሃሮ ሊሙ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጋሮማ ቶሎሳ ግድያው ስለመፈፀሙ ማረጋገጫ እንዳላቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።
"አባቴ ፈይሳ ዲሳሳ፣ ወንድሙ ዲንሳ ዲሳሳን ጨምሮ ስምንት የአጎቶቼ ልጆችን አጥተናል። ግድያው በጣም አሰቃቂ ነበር" ይላሉ አቶ ዋጋሪ።
በተመሳሳይ እለት የቤተሰብ አባላቱን ግድያ ጨምሮ በያሶ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት አርባ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ኗሪዎችና የአዋሳኝ ወረዳ አስተዳዳሪው ቢናገሩም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊው አቶ ሙሳ ግን አስር ሰው ብቻ ስለመገደሉ መረጃ እንዳላቸው ይገልፃሉ።
ሆኖም ግን ጉዳዩን በሚመለከት ተጨማሪ መረጃ እንደሚያስፈልጋቸው "መንገድ በመዘጋቱ ነገሮችን በቅርበት ማጣራት አልቻልንም" በማለት ተናግረዋል።
አቶ ሙሳ እንደሚሉት የረቡዕ ጥቃት ከመፈፀሙ ከጥቂት ቀናት በፊት ሁለት የመንግሥት ሰራተኞች ተገድለዋል። አርብ እለትም ደግሞ በካማሼ ሌሎች ሦስት ሰዎች መሞታቸውንም ገልፀዋል።
በያሶ ጥቃቱን የፈፀሙት ታጣቂዎች ከመሆናቸው በዘለለ ስለታጣቂዎቹ እስካሁን ምንም የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለ አቶ ሙሳ ይናገራሉ።
'ያፈነገጡ የኦነግ ታጣቂዎች' ለአካባቢው ስጋት እየሆኑ እንደሆነ አቶ ሙሳ ቢናገሩም ያነጋገርናቸው ኗሪዎች እና የአዋሳኝ ወረዳ ሃላፊዎች ግን በአካባቢው #የኦነግ ታጣቂ እንደሌለ ገልፀዋል።
በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ አራት የካማሺ ዞን ሃላፊዎች አሶሳ ከተማ ስብሰባ ቆይተው ወደ ካማሺ በመመለስ ላይ ሳሉ በተከፈተባቸው ተኩስ ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ብዙዎች መገደላቸውንና ወደ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ከቀያቸው መፈናቀላቸው ይታወሳል።
በአሁኑ ወቅት ግን ነገሮችን #ለመቆጣጠር በያሶ ከተማ ፌደራል ፖሊስ፤ በካማሽ ደግሞ መከላከያ ሠራዊት እንደገባ አቶ ሙሳ ገልፀዋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
ሀጫሉ ሁንዴሳ...
“•••እነኚህ ሰዎች ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ሰርተው #ያስደመሙኝ ነገር አለ። ከዚህ በፊት ኦሮሞ እንደ አገር አፍራሽ ተደርጎ ብዙ ተሰርቶበታል። አሁን ግን ኦሮሞ አገር አፍራሽ እንዳልሆነ፣ ትልቅ ሃሳብ ያለው እንጂ የሚያሳስብ እንዳልሆነ፣ ያገሪቱ ጋሻ እንደሆነ ባለም ላይ አስመስክረዋል። በእርግጥ ሁሉም ነገር ተሟልቶ ተጠናቋል ማለት አይደለም። #ለዘመናት የተተበተበብንን ትብታብ በጣጥሶ ነገሮችን ለማስተካከል #አይደለም ስምንት ወር #ስምንት አመትም አይበቃም። አሁን የታሰርንበትን እስራቶችን (ቋጠሮዎችን) በመፍታት ደረጃ ላይ ነው ያሉት። ደግሞም #ሁሉንም ነገር ከነሱ ብቻ መጠበቅ የለብንም። #እኛም እጅ ለእጅ ተያይዘን የምንሰራቸው ነገሮች አሉ።”
ሀጫሉ ሁንዴሳ ከOBN ቴሌቪዝን ጋር በነበረው ቆይታ የተናገረው!
©Daniel Ragassa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
“•••እነኚህ ሰዎች ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ሰርተው #ያስደመሙኝ ነገር አለ። ከዚህ በፊት ኦሮሞ እንደ አገር አፍራሽ ተደርጎ ብዙ ተሰርቶበታል። አሁን ግን ኦሮሞ አገር አፍራሽ እንዳልሆነ፣ ትልቅ ሃሳብ ያለው እንጂ የሚያሳስብ እንዳልሆነ፣ ያገሪቱ ጋሻ እንደሆነ ባለም ላይ አስመስክረዋል። በእርግጥ ሁሉም ነገር ተሟልቶ ተጠናቋል ማለት አይደለም። #ለዘመናት የተተበተበብንን ትብታብ በጣጥሶ ነገሮችን ለማስተካከል #አይደለም ስምንት ወር #ስምንት አመትም አይበቃም። አሁን የታሰርንበትን እስራቶችን (ቋጠሮዎችን) በመፍታት ደረጃ ላይ ነው ያሉት። ደግሞም #ሁሉንም ነገር ከነሱ ብቻ መጠበቅ የለብንም። #እኛም እጅ ለእጅ ተያይዘን የምንሰራቸው ነገሮች አሉ።”
ሀጫሉ ሁንዴሳ ከOBN ቴሌቪዝን ጋር በነበረው ቆይታ የተናገረው!
©Daniel Ragassa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቡ ወረዳ #በህጻናት የአካል ክፍሎች ዝርፊያ ላይ ተሰማርተዋል በሚል መሰረተ-ቢስ መረጃ ተነሳስተው ሰላማዊ ሰዎች ላይ ግድያ የፈጸሙ #ስምንት/8/ ግለሰቦችን መያዙን የወረዳው ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ አህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት በህብረተሰቡ ዘንድ በየጊዜው የሚሰራጨው ምንጩ ያልታወቀ የተሳሳተ መረጃ የአካባቢውን ሰላም እያወከው ይገኛል።
በዚህ የተነሳም ከትላንት በስቲያ ምሽት በወረዳው ቀበሌ 029 ላይ ቤተሰባቸውን ጠይቀው በመመለስ ላይ የነበሩ አምስት ግለሰቦች የህጻናት አካል ስርቆት ላይ የተሰማሩ ናቸው በሚል መሰረተ-ቢስ ጥርጣሬ መነሻነት በተፈጸመባቸው #የደቦ ድብደባ ህይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።
በድብደባው ህይወታቸው ካለፈው ግለሰቦች መካከል የሶስቱ አስከሬን ወደ ቤተሰቦቻቸው የተላከ ሲሆን ቤተሰቦቻቸው ያልተገኙ ሁለት አስከሬኖች አስፈላጊው መረጃ ተመዝግቦ በዛሬው እለት የቀብር ስነ-ስርዓታቸው እንደሚፈጸም ገልፀዋል።
በድርጊቱ የተጠረጠሩ ስምንት ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳዩ እየተጣራ ሲሆን ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ለማዋል ከህብረተሰቡ ጋር እየተሰራ መሆኑንም ኮማንደር መሀመድ ተናግረዋል፡፡
በትላንትናው እለትም ከህብረተሰቡ፤ ከሐይማኖት አባቶች፤ ከሃገር ሽማግሌዎች ጋር በተደረገዉ ዉይይት ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በማጋለጥ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተባብረው ለመስራት ስምምነት ላይ ተድርሷል”ብለዋል።
ህብረተሰቡም በእንዲህ አይነት መሰረተ-ቢስ ወሬ ሳይታለል ሁኔታውን በማጣራት ከደቦ ፍርድ እንዲቆጠብ መክረዋል፡፡
ለውጡን ለማደናቀፍ የሐሰት ወሬ እየነዙ የወረዳውን ሰላም ለማወክ የሚሰሩ ኃይሎች ስላሉ ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅ በእያንዳንዱ ጉዳይ ምክንያታዊ እንዲሆንም ጠይቀዋል፡፡
Via #ENA
የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ አህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት በህብረተሰቡ ዘንድ በየጊዜው የሚሰራጨው ምንጩ ያልታወቀ የተሳሳተ መረጃ የአካባቢውን ሰላም እያወከው ይገኛል።
በዚህ የተነሳም ከትላንት በስቲያ ምሽት በወረዳው ቀበሌ 029 ላይ ቤተሰባቸውን ጠይቀው በመመለስ ላይ የነበሩ አምስት ግለሰቦች የህጻናት አካል ስርቆት ላይ የተሰማሩ ናቸው በሚል መሰረተ-ቢስ ጥርጣሬ መነሻነት በተፈጸመባቸው #የደቦ ድብደባ ህይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።
በድብደባው ህይወታቸው ካለፈው ግለሰቦች መካከል የሶስቱ አስከሬን ወደ ቤተሰቦቻቸው የተላከ ሲሆን ቤተሰቦቻቸው ያልተገኙ ሁለት አስከሬኖች አስፈላጊው መረጃ ተመዝግቦ በዛሬው እለት የቀብር ስነ-ስርዓታቸው እንደሚፈጸም ገልፀዋል።
በድርጊቱ የተጠረጠሩ ስምንት ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳዩ እየተጣራ ሲሆን ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ለማዋል ከህብረተሰቡ ጋር እየተሰራ መሆኑንም ኮማንደር መሀመድ ተናግረዋል፡፡
በትላንትናው እለትም ከህብረተሰቡ፤ ከሐይማኖት አባቶች፤ ከሃገር ሽማግሌዎች ጋር በተደረገዉ ዉይይት ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በማጋለጥ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተባብረው ለመስራት ስምምነት ላይ ተድርሷል”ብለዋል።
ህብረተሰቡም በእንዲህ አይነት መሰረተ-ቢስ ወሬ ሳይታለል ሁኔታውን በማጣራት ከደቦ ፍርድ እንዲቆጠብ መክረዋል፡፡
ለውጡን ለማደናቀፍ የሐሰት ወሬ እየነዙ የወረዳውን ሰላም ለማወክ የሚሰሩ ኃይሎች ስላሉ ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅ በእያንዳንዱ ጉዳይ ምክንያታዊ እንዲሆንም ጠይቀዋል፡፡
Via #ENA
❤1