TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢህአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ በሀገር #ደህንነት እና #ሰላም ጉዳይ ላይ #ጠንካራ ውሳኔዎች እንደሚያሳልፍ እምነቴ ነው። ከዚህ በኋላ ችግር እና መከራ የምንሰማበት ጊዜ ማብቃት አለበት።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጄነራል ብርሃኑ ጁላ‼️

በምዕራብ ኦሮሚያ ከፍተኛ የፀጥታ ችግር መከሰቱን እና አሁን ግን #በቁጥጥር_ሥር እየዋለ መሆኑን የጦር ኃይሎች ምክትል ኤታማዦር ሹም አስታወቁ። ጀነራል #ብርሃኑ_ጁላ ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ በተጠቀሰው አካባቢ ተስፋ ሰንቆ ከውጭ የገቡ አካላትን የተቀበለው ሕዝብ መልሶ ለከፍተኛ ጉዳት መዳረጉን አመልክተዋል። አሁን እየተወሰደ ባለው #ጠንካራ_እርምጃ አማካኝትም የተዘጉ መንገዶች እና አደጋ ላይ የወደቁ የመንግሥት የመዋቅር ሥፍራዎች መከፈታቸውንም ዘርዝረዋል።

ከተማዎቹን እየዞሩ ያተራምሱ ነበር ያሏቸው አባ ቶርቤ በሚል መጠሪያ የሚታወቁ ኃይሎችም በመንግስት ቁጥጥር ሥር መግባታቸውንም ምክትል ኤታማዦር ሹሙ ገልጸዋል።

«አሁን #ትጥቅ_ማስፈታት ጀምረናል፤ እነዚያ የተዘጉ ከተሞች ነጻ አውጥተናቸዋል። የተዘጉ መንገዶች ተከፍተዋል፤ ሰዎች እንደተዘረፉ አውቃለሁ፤ ሸሽተው አዲስ አበባ የገቡ እንዳሉ አውቃለሁ፤ አባ ቶርቤ የሚባል በየከተማው እየዞረ ነፍስ የሚገድል ፤ የሚያስፈራራ ይሄን ለቅመነዋል።» ብለዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ከሰሞኑ በተከሰተው ወቅታዊ ሁኔታ መከላከያ ሰው አልገደለም ያሉት ጀነራሉ ክስተቱ #እንዲጣራ መወሰኑን፤ ድርጊቱ ተፈፅሞም ከሆነ መከላከያ ይቅርታ እንደሚጠይቅ #ካሳም እንደሚከፍል አመልክተዋል። ባለሥልጣኑ በተለያዩ አካባቢዎች ስለደረሰዉ ጉዳት ምንም አይነት አሃዛዊ መረጃ መስጠት እንደማይፈልጉ ገልፀዋል።

ምንጭ፦ DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ክቡር ፕረዝዳንት ለማ መገርሳ #ኢፍትሃዊነት እና #የአሻጥር ፖለቲካን የሚጸየፉ፣ በህዝቦች ወንድማማችነት፣ እኩልነት እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በጽኑ የሚያምኑ ይንንም በተግባር ታግለዉ #ጠንካራ ሥብዕናቸዉን በተግባር ያረጋገጡ የህዝብ ልጅ ናቸዉ፡፡" አቶ አዲሱ አረጋ
.
.
.
ሠሞኑን አንዳንድ #አክቲቪስቶች እና ፖለቲከኞች የክቡር ፕረዝዳንት ለማ መገርሳን ንግግሮች ከተነገረበት አዉድ ዉጪ እና ትርጉም ጭምር አጣምመዉ በማቅረብ ፕረዝዳንት ለማን የአሻጥር ፖለቲካ አራማጅ አስመስለዉ በማቅረብ የማጥላላት ዘመቻቸዉን ተያይዘዉታል፡፡ ለአብነትም በአንድ መድረክ ስለ ከተማ ዲሞግራፊ የተነገረዉን ንግግር በአሻጥር ፖለቲካ ተርጉመዉ እያራገቡት ይገኛሉ፡፡

በዚህ መድረክ አንዱ ተሳታፊ በኦዲፒ የእስካሁን አጠቃላይ እንቅስቃሴ የኦሮሞ ህዝብ በኢኮኖሚ ሆነ በማህበራዊ እድገቱ እምብዛም እንዳልተሻሻለ አሁንም በገጠር በሞፈር እና ቀንበር እያረሰና የከብት ጭራ እየተከተለ እየኖረ እንደሆነ፣ ኦሮሞነት በገጠር እና በኋላ ቀር ኑሮ እየተመሰለ ነዉ የሚል ጠንከር ያለ ትችት አዘል ጥያቄ ከአንድ ተሳታፊ ለክቡር ፕረዝዳንቱ ተነስቶ ነበር፡፡ ለዚህም ጥያቄ ፕረዝዳንት ለማ ማብራሪያ ሲሰጡ ይህንን ችግር እንደ ፓርቲ ለመቀየር መስራት አለብን ከሚል ቅን ሀሳብ በመነሳት ኦሮሞነት በኋላ ቀር እና በገጠሬነት ብቻ ሳይሆን የከተማ ዘመናዊ ኑሮም መገለጽ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ በዚህም ረገድ ኦዲፒ ጠንክሮ በመስራት ላይ እንደሚገኝና ከኢትዮጵያ ሶማሌ በኦሮሞነታቸዉ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን ጭምር በኦሮሚያ ከተሞች በህዝቡ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲሰፍሩና የከተማ የኑሮ ዘይቤን እንዲለማመዱ መደረጉን፤ የልማት ተነሽ አርሶ አደሮች እና የአርሶ አደር ልጆች በከተማ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታን እንዲያገኙ መደረጉን፤ በኦሮሚያ ከተሞች የኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ ኑሮ እየተሰባጠረ መምጣቱን፤ ወደ ፊትም የኦሮሞ የስነ ህዝብ ስብጥር (ዲሞግራፊ) በገጠር ብቻ ተወስኖ መቅረት እንደሌለበትና ህዝባችን በከተማም መኖር እንዳለበት ለዚህም ኦዲፒ ጠንክሮ እንደሚሰራ አጥብቀዉ ምላሽ ሠጥተዋል፡፡

የሚገርመዉ ጉዳይ ኦሮሞ ህዝብ አኗኗር በኋላ ቀር የገጠር ኑሮ ብቻ መታወቅ የለበትም፣ ህዝባችን ኑሮዉ መሻሻል አለበት ገጠርም ከተማም መኖር አለበት የሚል ሃሳብ እንዴት የአሻጥር ፖለቲካ ሊሆን ይችላል? የኦሮሞን ህዝብ ኑሮ ለማሻሻል እና ወደ ከተሜነት ማዘመን የክልሉ መንግስት ግዴታ ነዉ፡፡ ለዚህ ደግሞ የክልሉ መንግስት የማንም ፈቃድ እና ቡራኬ አያሻዉም፡፡

ክቡር ፕረዝዳንት ለማ መገርሳ ኢፍትሃዊነት እና የአሻጥር ፖለቲካን የሚጸየፉ፣ በህዝቦች ወንድማማችነት ፣እኩልነት እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በጽኑ የሚያምኑ ይንንም በተግባር ታግለዉ ጠንካራ ሥብዕናቸዉን በተግባር ያረጋገጡ የህዝብ ልጅ ናቸዉ፡፡ አምርረዉ የሚጠሉትንና ሲታገሉት የነበረዉን የሴራ እና የአሻጥር ፖለቲካ በማራማድ የኦሮሞን ህዝብም ሆነ በግላቸዉ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት የሚያስብ ስብዕና ፈጽሞ የላቸዉም፡፡

ነገር ግን ፕረዝዳንት ለማ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ፕረዝዳንት እንደመሆናቸዉ የኦሮሞን ህዝብ ኑሮ ለመለወጥ መስራት ግዴታቸዉ እንደሆነም መዘንጋት የለበትም፡፡ ስለሆነም ፕረዝዳንቱ የኦሮሞን ህዝብ የልማት እና የለዉጥ አጀንዳዎች ባነሱ ቁጥር በአሻጥር ለመክሰስ መሯሯጥ ኢ-አመክኖአዊ እና ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡

#AddisuArega

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#StopHateSpeech🔝

የትላንት ምሽቱ የTIKVAH_ETHIOPIA #STOP_HATE_SPEECH 3ኛው መድረክ እጅግ በጣም በተሳካ ሁኔታ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶክተር #ታከለ(WSU) በተገኙበት ተካሂዷል። ዶክተር ታከለ #ለመላው ሀገራችን ህዝብ የሚሆኑ #ጠንካራ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል። የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላትም በቀጣይ ስራዎች ላይ ውይይት አድርገዋል።

⌚️ምሽት 1:30 የዶክተሩን ንግግር ጨምሮ ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን አቀርብላችኃለሁ!!

ማስታወሻ🗓

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ #StopHateSpeech የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ስለሚኖር ተዘጋጁ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia