TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
* Update

የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ከኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጋር መነጋገራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳውቋል።

ሐመር በዚሁ ወቅት ጦርነት በአስቸኳይ ቆሞ ፤ በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ወደ ሰላም ድርድር ማምራት እንደሚያስፈልግ መወያየታቸውን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።

ሐመር ከህወሓት ሊቀመምበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር እንዴት/በምን ተገናኝተው እንደተነጋገሩ ባይገለፅም ለእሳቸውም ጦርነት በአስቸኳይ ቆሞ በአፍሪካ ህብረት መሪነት ወደ ሰላም ድርድር ማምራት እንደሚያስፈልግ እንዳስገነዘቧቸው ተገልጿል።

እንደ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም እና ወደ ድርድር ለመግባት በመጪዎቹ ቀናት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ፀሀፊ ሞሊ ፊ ፣ አምባሳደር ማይክ ሀመር እና ሌሎችም የአሜሪካ ዲፕሎማቶች ከአፍሪካ ህብረት እንዲሁም ከቀጠናው ቀልፍ ናቸው ከሚባሉት ተዋናዮች ተመድ ፣ አውሮፓ ህብረት ፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ልዑካን ጋር ይመክራሉ።

መስሪያ ቤቱ ፤ የአሜሪካ ዓላማ በኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል ያለው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ፤ ኤርትራም ወደ ድንበሯ እንድትመለስ ዴፕሎማሲያዊ ግፊት ማድረግ ነው ብሏል።

ለግጭቱ ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለውም ያለው የአሜሪካ መንግስት መፍትሄድ በሁሉም ወገን ዘንድ የሰላም ድርድር ማድረግ ብቻ ነው ብሏል።

አሜሪካ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ለኢትዮጵያ #አንድነት#ሉዓላዊነት#የግዛት_አንድነት ቁርጠኛ አቋም አለኝ ስትልም በድጋሚ ማረጋገጧን ቪኦኤ ሬድዮ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
👍521👎18416🥰9😢9😱2