TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጥንቃቄ አድርጉ‼️

#ከኢትዮጵያ ወደ #ቻይና የምትሄዱ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ሰዎች ይህን እቃ እዛ ላለ ሰው አድርስልኝ/አድርሺልኝ ሲሏችሁ በደንብ የሚላከውን ነገር ፈትሹ። ቻይና ከሚገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ለመረዳት እንደቻልነው አንዳንዶች በሚላከው እቃ ውስጥ አደንዛዥ እፆችን በመጨመር እንደሚልኩ ጠቁመዋል። በተለይ ምግብ ነክ ነገሮች ውስጥ የአደንዛዥ እፆችን በመክተት ይልካሉ። ወዳጆቻችን ሳታውቁት በወንጀል እንዳትጠየቁ ቅድመ ጥንቃቄ አድርጉ።

ለማሳያነት፦ ባለፈው ሳምንት አንዲት ኢትዮጵያዊ በኤርፖርት ስትፈተሽ ያልተገቡ ነገሮችን ይዛ በመገኘቷ ለእስር ተዳርጋለች (ሰው አድርሽልኝ ብሏት) እንዲሁም አንድ ኢትዮጵያዊ ከወራት በፊት በተመሳሳይ ለእስር ተዳርጓል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኤርትራ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 65 ደረሱ! በኣዲባራ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ከሚገኙ ከውጭ ተመላሾች መካከል ሃያ አራት (24) ሰዎች /ከሱዳን የተመለሱ/ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው መረጋገጡን የኤርትራ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ ምሽት አሳውቋል። በአጠቃላይ በሀገሪቱ ስልሳ አምስት (65) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን ከነዚህ መካከል ሰላሳ ዘጠኝ (39) ሰዎች ከበሽታው…
በኤርትራ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 96 ደርሰዋል!

የኤርትራ ጤና ሚኒስቴር በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጡ 31 ሰዎች ማግኘቱን በትላንትናው ዕለት ማስታወቁን #BBC ዘግቧል።

ሚንስቴሩ እንዳስታወቀው 31ዱ ሰዎች የተገኙት የአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ጊዜያቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ነው።

ቫይረሱ የተገኘባቸው 30 ሰዎች በቅርቡ ከሱዳን የተመለሱ ኤርትራውያን ሲሆን አንዱ (1) ደግሞ #ከኢትዮጵያ የተመለሰ ኤርትራዊ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Somalia #SW

ሀሰን ኢብራሂም ሉግቡር ተገደሉ።

የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ክልል ፍትህ ሚኒስትር ሀሰን ኢብራሂም ሉግቡር በባይዶዋ ከነ ልጃቸው በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ተገደሉ።

ሚኒስትሩ የተገደሉት ዛሬ ዓርብ ዕለት ከመስጂድ ሲወጡ በተፈፀመ ጥቃት ነው።

በጥቃቱ ሌሎች 11 ሰዎችም ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።

የደቡብ ምዕራብ ክልል ፕሬዜዳንት አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ ግድያውንና ጥቃቱን አውግዘው ከጥቃቱ ጀርባ የአልሸባብ የሽብር ቡድን መኖሩን አመልክተዋል።

ይህ ጥቃት በያዝነው ወር እኤአ በቀን 27 በታችኛው ሸበል ክልል የማርካ ወረዳ አስተዳዳሪ አብዱላሂ አሊ ዋፎውን ጨምሮ ከ10 በላይ ሰዎችን ከገደለው የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት እንዲሁም በአፍጎዬ ከተማ ፍንዳታ ተከስቶ ቢያንስ አራት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ከቆሰሉበት ጥቃት ከቀናት በኃላ የተፈፀመ ነው።

በሌላ በኩል፤ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ዛሬ #ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰነው የሶማሊያዋ የድንበር ከተማ " አቶ " ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ከፍቶ እንደነበር ቢቢሲ ሶማልኛ ዘግቧል።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልወደዱ የሶማሌ ክልል ባለሥልጣን በሰጡት ቃል ፤ የሽብር ቡድኑ አቶ ላይ በ2 ሳምንት ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ ጥቃት መሰንዘሩን ይህን ተከትሎ ውጊያ መካሄዱን አመልክተዋል።

ዛሬ ወደ አቶ ዘልቆ ጥቃት የመፈጸም ዓላማ የነበረው የአልሻባብ ታጣቂ ኃይል፤ ያሰበው ሳይሳካ #ሽንፈት እንዳጋጠመው ተናግረዋል።

በፀጥታ ኃይሎችም በኩል ጉዳት መድረሱን ያመለከቱት ባለስልጣኑ ለጊዜው ዝርዝር መናገር አልችልም ብለዋል።

አልሸባብ ከጥቂት ቀናት በፊት ኢትዮጵያን ለመዳፈር ሞክሮ በሶማሌ ልዩ ኃይል ክፉኛ መመታቱ አይዘነጋም። አሁንም በድንበር የተጠናከረ ጥበቃ መኖሩን ለማወቅ ችለናል።

@tikvahethiopia
👍514😢8315👏14🙏9🥰8