TIKVAH-ETHIOPIA
#KOBO የኢትዮጵያ መከላከያ " ቆቦ " ን ለቆ መውጣቱን መንግስት ገለፀ። የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ " አሻባሪው ህወሓት የሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም የቆቦ ከተማን ከውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው " ብሏል። በሌላ በኩል ደግሞ በከተማ ውስጥ ሠርጎ ገቦችን በማሥረግ የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ…
#ወልድያ
የወልድያ ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላለፈ።
የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።
" የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው " ያለው የወልድያ ከተማ " የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
ከተማ አስተዳደሩ " የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም " ያለ ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።
የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት መሆኑን አመልክቷል።
ምንም እንኳን አሁንም መሳሪያ ወርዶ ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ እየቀረቡ ቢሆንም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። ህወሓት ከዚህ ቀደም ለሰብዓዊነት ሲባል ተኩስ አቁም በታወጀበት ወቅት ከነበረበት ቦታ ወደፊት በመምጣት የአማራ ክልል ቦታዎችን እየያዘ ነው።
በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ መንግስት እንደተገለፀው የኢትዮጵያ መከላከያ ከቆቦ ከተማ ለቆ ወጥቷል፤ በዚህም ቆቦ በህወሓት ስር ይገኛል።
መንግስት ፤ ህወሓት #የህዝብ_ማዕበል ስልት በመጠቀም ጥቃት እያደረሰ መሆኑን በመግለፅ የህዝብ ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ መከላከያው " ቆቦ " ን መልቀቁን በትለንትናው መግለጫ ማስረዳቱ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የወልድያ ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላለፈ።
የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።
" የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው " ያለው የወልድያ ከተማ " የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
ከተማ አስተዳደሩ " የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም " ያለ ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።
የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት መሆኑን አመልክቷል።
ምንም እንኳን አሁንም መሳሪያ ወርዶ ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ እየቀረቡ ቢሆንም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። ህወሓት ከዚህ ቀደም ለሰብዓዊነት ሲባል ተኩስ አቁም በታወጀበት ወቅት ከነበረበት ቦታ ወደፊት በመምጣት የአማራ ክልል ቦታዎችን እየያዘ ነው።
በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ መንግስት እንደተገለፀው የኢትዮጵያ መከላከያ ከቆቦ ከተማ ለቆ ወጥቷል፤ በዚህም ቆቦ በህወሓት ስር ይገኛል።
መንግስት ፤ ህወሓት #የህዝብ_ማዕበል ስልት በመጠቀም ጥቃት እያደረሰ መሆኑን በመግለፅ የህዝብ ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ መከላከያው " ቆቦ " ን መልቀቁን በትለንትናው መግለጫ ማስረዳቱ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
👍1.35K👎928😢248😱75🥰40👏36❤30
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ወልድያ
ወልድያ ከተማ ሠላማዊ እንቅስቃሴዋ እንደቀጠለ መሆኑን የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።
የተለያዩ ሚዲያዎች እና የፖለቲካ ተንታኝ ነን የሚሉ የውጭ አካላት በማህበራዊ ሚዲያው ወልድያን በተመለከተ ሀሰተኛ ዜና እያሰራጩ ይገኛሉ።
" ከወልድያ አመራሩ ወጥቷል፣ ወልድያንም ህወሓት ይዟል " የሚሉ መረጃዎችን ቢያሰራጩም ሁሉም ሀሰት መሆኑና ህዝቡን ለማሸበር የሚሰራ ስራ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ግጭት በተለያዩ ከተሞች ተመሳሳይ አይነት በሀሰት ህዝብን የማሸበር ስራ ሲሰራ፣ ህዝብን ለማስደንገጥ ብዙ ጥረቶች ሲደረጉና በዚህ ሳቢያ ብዙ መመሰቃቀል ሲፈጠር እንደነበር አይዘነጋም።
እስካሁን ድረስ በወልድያና በቀጠናው ባለው ሁኔታ ከወልድያ ከተማም ይሁን ከጅቡቲ ወደብ የሚነሱ አገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎችን ከተለመደው የዕለት ተዕለት ጉዟቸው ያስተጓጎላቸው ሁኔታ እንዳልተከሰተ ከወልድያ ከተማ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በሌላ በኩል ደግሞ ፤ በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ከሚማሩ ተማሪዎች ከወቅቱ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ስጋት አድሮባቸው ግቢያቸውን ለቀው የወጡ፤ የትራንስፖርት አጥተውም በእግር የተጓዙ እንዳሉ ለማወቅ ችለናል።
አንዳንድ መልዕክት የላኩ የግቢው ተማሪዎች ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ " ወደ መጡበት አካባቢ እንዲመለሱ እንዲደረግ ፤ አሁን በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ሁኔታ እነሱም ቤተሰብም ጭምር ጭንቀት ላይ በመሆኑና በዚህ ሁኔታ ትምህርትን በንቃት መከታተል ስለሚያስቸግር ተቋማቸው መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል።
በተማሪዎቹ ስጋት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው ምላሽ ለማግኘት እንጥራለን።
@tikvahethiopia
ወልድያ ከተማ ሠላማዊ እንቅስቃሴዋ እንደቀጠለ መሆኑን የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።
የተለያዩ ሚዲያዎች እና የፖለቲካ ተንታኝ ነን የሚሉ የውጭ አካላት በማህበራዊ ሚዲያው ወልድያን በተመለከተ ሀሰተኛ ዜና እያሰራጩ ይገኛሉ።
" ከወልድያ አመራሩ ወጥቷል፣ ወልድያንም ህወሓት ይዟል " የሚሉ መረጃዎችን ቢያሰራጩም ሁሉም ሀሰት መሆኑና ህዝቡን ለማሸበር የሚሰራ ስራ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ግጭት በተለያዩ ከተሞች ተመሳሳይ አይነት በሀሰት ህዝብን የማሸበር ስራ ሲሰራ፣ ህዝብን ለማስደንገጥ ብዙ ጥረቶች ሲደረጉና በዚህ ሳቢያ ብዙ መመሰቃቀል ሲፈጠር እንደነበር አይዘነጋም።
እስካሁን ድረስ በወልድያና በቀጠናው ባለው ሁኔታ ከወልድያ ከተማም ይሁን ከጅቡቲ ወደብ የሚነሱ አገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎችን ከተለመደው የዕለት ተዕለት ጉዟቸው ያስተጓጎላቸው ሁኔታ እንዳልተከሰተ ከወልድያ ከተማ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በሌላ በኩል ደግሞ ፤ በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ከሚማሩ ተማሪዎች ከወቅቱ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ስጋት አድሮባቸው ግቢያቸውን ለቀው የወጡ፤ የትራንስፖርት አጥተውም በእግር የተጓዙ እንዳሉ ለማወቅ ችለናል።
አንዳንድ መልዕክት የላኩ የግቢው ተማሪዎች ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ " ወደ መጡበት አካባቢ እንዲመለሱ እንዲደረግ ፤ አሁን በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ሁኔታ እነሱም ቤተሰብም ጭምር ጭንቀት ላይ በመሆኑና በዚህ ሁኔታ ትምህርትን በንቃት መከታተል ስለሚያስቸግር ተቋማቸው መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል።
በተማሪዎቹ ስጋት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው ምላሽ ለማግኘት እንጥራለን።
@tikvahethiopia
👍1.03K👎85❤38👏36😢36🥰18😱13🕊2