#ኮማንድ_ፖስት
በደቡብ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች ተፈጥሮ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን በክልሉ የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ። ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ በዛሬው እለት ዝርዝር ተግባራትን እና የአፈጻጸም ሁኔታዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚህም በክልሉ በተለይም በሲዳማ ዞን እና አካባቢው ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር በተያያዘ በደረሰው ጉዳት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆኑን አስታውቋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ላይ የመለየትና የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው ያለው ኮማንድ ፖስቱ፥ ህብረተሰቡም ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ የመስጠትና ንብረቶችን የማስመለስ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
ከህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘም ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ጠቅሶ፥ የፍተሻ ኬላዎችን አልፈው በግለሰቦች እጅ የሚገኙ መሳሪያዎች ተይዘዋልም ነው ያለው።
ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ከ12 ቀናት በፊት በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ችግር መከሰቱን ተከትሎ መቋቋሙ የተገለጸ ሲሆን፥ ክልሉ ወደ ቀደመ ሰላሙ እስከሚመለስ ድረስ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/CMP-07-31
በደቡብ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች ተፈጥሮ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን በክልሉ የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ። ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ በዛሬው እለት ዝርዝር ተግባራትን እና የአፈጻጸም ሁኔታዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚህም በክልሉ በተለይም በሲዳማ ዞን እና አካባቢው ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር በተያያዘ በደረሰው ጉዳት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆኑን አስታውቋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ላይ የመለየትና የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው ያለው ኮማንድ ፖስቱ፥ ህብረተሰቡም ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ የመስጠትና ንብረቶችን የማስመለስ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
ከህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘም ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ጠቅሶ፥ የፍተሻ ኬላዎችን አልፈው በግለሰቦች እጅ የሚገኙ መሳሪያዎች ተይዘዋልም ነው ያለው።
ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ከ12 ቀናት በፊት በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ችግር መከሰቱን ተከትሎ መቋቋሙ የተገለጸ ሲሆን፥ ክልሉ ወደ ቀደመ ሰላሙ እስከሚመለስ ድረስ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/CMP-07-31
#ኮማንድ_ፖስት
ሀምሌ 11 ቀን 2011 ዓም #በሲዳማ_ዞን እና #በሀዋሳ ከተማ የተከሰተውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ በክልሉ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት መደበኛውን የህግ ማስከበር ስርዓት ተከትሎ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ኮማንድ ፖስቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራትን አስመልክቶ ዛሬ በሀዋሳ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/CM-07-31
ሀምሌ 11 ቀን 2011 ዓም #በሲዳማ_ዞን እና #በሀዋሳ ከተማ የተከሰተውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ በክልሉ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት መደበኛውን የህግ ማስከበር ስርዓት ተከትሎ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ኮማንድ ፖስቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራትን አስመልክቶ ዛሬ በሀዋሳ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/CM-07-31
#ኮማንድ_ፖስት፦
√መደበኛ ህጎችን መጣስ
√ያልተፈቀዱ ሰልፎችን ማድረግ፣
√በዜጎች ላይ ሰብዓዊ ጥቃት መፈጸም፣
√የተለየ እና የሰላም ማደፍረስ እንቅስቃሴ ማሳየትና ማድረግ በኮማንድ ፖስቱ ተከልክለዋል።
ከዚህ ባለፈም...
በሃዋሳ ከተማ ክልከላው እስከሚነሳ ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር አይቻልም። ከዚህ ጋር ተያይዞ ሞተር ብስክሌታቸው የተያዘባቸው ግለሰቦች ባለቤትነታቸውን አሳውቀው መውሰድ ይችላሉ ነው ብሏል ኮማንድ ፖስቱ።
በቀጣይም ከሃዋሳ ውጭ ባሉ ሌሎች ከተሞች ከሞተር ብስክሌት አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ለፀጥታ ችግር ሊሆኑ የሚችሉ እንቅስቃሴዎች ከተስተዋሉ ክልከላ ይደረጋል።
ከላይ ከተጠቀሰው ውጭ በኮማንድ ፖስቱ የሰዓት እላፊም ሆነ የተለየ ክልከላ አልተደረገም፤ ኮማንድ ፖስቱ፥ ወደፊት ከዚህ ጋር ተያይዞ የተለዩ አካባቢዎች ካሉ ይፋ ይደረጋል።
🏷አሁን ላይ በክልሉ ሁሉም መንገዶች ክፍት መሆናቸውን ተጠቅሷል፥ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ላሳየው ትብብር ምስጋና ቀርቧል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
√መደበኛ ህጎችን መጣስ
√ያልተፈቀዱ ሰልፎችን ማድረግ፣
√በዜጎች ላይ ሰብዓዊ ጥቃት መፈጸም፣
√የተለየ እና የሰላም ማደፍረስ እንቅስቃሴ ማሳየትና ማድረግ በኮማንድ ፖስቱ ተከልክለዋል።
ከዚህ ባለፈም...
በሃዋሳ ከተማ ክልከላው እስከሚነሳ ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር አይቻልም። ከዚህ ጋር ተያይዞ ሞተር ብስክሌታቸው የተያዘባቸው ግለሰቦች ባለቤትነታቸውን አሳውቀው መውሰድ ይችላሉ ነው ብሏል ኮማንድ ፖስቱ።
በቀጣይም ከሃዋሳ ውጭ ባሉ ሌሎች ከተሞች ከሞተር ብስክሌት አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ለፀጥታ ችግር ሊሆኑ የሚችሉ እንቅስቃሴዎች ከተስተዋሉ ክልከላ ይደረጋል።
ከላይ ከተጠቀሰው ውጭ በኮማንድ ፖስቱ የሰዓት እላፊም ሆነ የተለየ ክልከላ አልተደረገም፤ ኮማንድ ፖስቱ፥ ወደፊት ከዚህ ጋር ተያይዞ የተለዩ አካባቢዎች ካሉ ይፋ ይደረጋል።
🏷አሁን ላይ በክልሉ ሁሉም መንገዶች ክፍት መሆናቸውን ተጠቅሷል፥ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ላሳየው ትብብር ምስጋና ቀርቧል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia