TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፍርድ ቤት በዋስ ከእስር እንዲፈቱ የወሰነላቸው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ እና ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ከእስር አልተለቀቁም። ዛሬ ግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት፣ 3ቱ ጋዜጠኖች በ10 ሺ ብር ዋስ እንዲለቀቁ መወሰኑ ይታወሳል። ነገር ግን መርማሪ ፖሊስ ይግባኝ ለማለት ለ8 ሰዓት ቀጥሮ ነበር ሆኖም ችሎቱን የሚመሩት…
#ችሎት

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬ ላይ የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዛሬው ችሎት፤ ለ3ቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደው ዋስትና ውድቅ እንዲደረግ እና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

@tikvahethiopia
👍1😢1