TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Tigray

#ሰብዓዊነት ሲባል የግጭት ማቆም ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ #ከፍተኛ ነው የተባለው የሰብዓዊ እርድታ ወደ ትግራይ ተጓጉዟል።

አርብ ዕለት ከአፋር ሰመራ ከተማ 215 የምግብ እርዳታ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ አቅንተዋል።

የግብረ ሰናይ ተቋማት በትግራይ ክልል 5.2 ሚሊዮን ሰዎችን ለመመገብ በየሳምንቱ በ500 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተጫነ የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ክልሉ ሊደርስ እንደሚገባ እየገለፁ ይገኛሉ።

በሌላ በኩል ፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ትግራይ ክልል ገብተው በነዳጅ እጦት ምክንያት ቆመው የነበሩ ተሽከርካሪዎቹ ከትግራይ እየወጡ እንደሆነ በዚህ ሳምንት አመልክቷል።

ተሽከርካሪዎቹ ባለፈው ዓመት 2021 ወደ ክልሉ ገብተው የነበሩ ከድረጅቱ የተገኘው መረጃ ያመልክታል።

የተሽከርካሪዎቹ ከትግራይ ክልል መመለስ በሃገር አቀፍ ደረጃ ያለውን ሰብዓዊ አቅርቦት ለማሻሻል እንደሚያግዝም ድርስክቱ ገልጿል።

#ኤፒ #WFP

@tikvahethiopia
👍5