ሰሞነኛው የግብፅ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ዙሪያ :
#Djibouti
• የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ከጂቡቲ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ለመወያየት ዛሬ ማለዳ ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል፡፡
- የፕሬዚዳንቱ የጅቡቲ ጉብኝት በዓይነቱ የመጀመሪያ ነው ተብሏል።
- የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በጋራ ትብብር እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ታውቋል። በተለይም በፀጥታ ፣ በወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር የውይይቱ ዓላማ መሆኑ ተጠቁሟል።
- የግብፅና የጅቡቲ መሪዎች የጋራ በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እና ሀሳቦችን ለመለዋወጥም አቅደዋል፡፡
#Kenya
• ግብፅ እና ኬንያ በትናንትናው እለት ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
- በናይሮቢ የተፈረመው ስምምነት ዓላማ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረገው የሁለትዮሽ ትብብር አካል ነው።
- ግብፅ ከኬንያ ጋር ያደረገችው ወታደራዊ ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2021 በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት ጋር ያደረገችው አራተኛ ስምምነት ነው፡፡
- ከኬንያ በተጨማሪ ከሱዳን ፣ ከኡጋንዳ እን ከብሩንዲ ጋር ግብፅ ወታደራዊ ስምምነት ፈርማለች፡፡
#Sudan
• ግብፅ እና ሱዳን በትናንትናው ዕለት ለ 6 ቀናት የሚቆይ ሁለገብ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በሱዳን ጀምረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ጉዳይ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ውጥረት ውስጥ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የሚካሔደው ይህ ልምምድ ፣ የናይል ጠባቂዎች (Nile Protectors/ናይል ፕሮቴክተርስ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
#አልአይን
@tikvahethiopia
#Djibouti
• የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ከጂቡቲ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ለመወያየት ዛሬ ማለዳ ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል፡፡
- የፕሬዚዳንቱ የጅቡቲ ጉብኝት በዓይነቱ የመጀመሪያ ነው ተብሏል።
- የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በጋራ ትብብር እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ታውቋል። በተለይም በፀጥታ ፣ በወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር የውይይቱ ዓላማ መሆኑ ተጠቁሟል።
- የግብፅና የጅቡቲ መሪዎች የጋራ በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እና ሀሳቦችን ለመለዋወጥም አቅደዋል፡፡
#Kenya
• ግብፅ እና ኬንያ በትናንትናው እለት ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
- በናይሮቢ የተፈረመው ስምምነት ዓላማ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረገው የሁለትዮሽ ትብብር አካል ነው።
- ግብፅ ከኬንያ ጋር ያደረገችው ወታደራዊ ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2021 በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት ጋር ያደረገችው አራተኛ ስምምነት ነው፡፡
- ከኬንያ በተጨማሪ ከሱዳን ፣ ከኡጋንዳ እን ከብሩንዲ ጋር ግብፅ ወታደራዊ ስምምነት ፈርማለች፡፡
#Sudan
• ግብፅ እና ሱዳን በትናንትናው ዕለት ለ 6 ቀናት የሚቆይ ሁለገብ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በሱዳን ጀምረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ጉዳይ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ውጥረት ውስጥ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የሚካሔደው ይህ ልምምድ ፣ የናይል ጠባቂዎች (Nile Protectors/ናይል ፕሮቴክተርስ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
#አልአይን
@tikvahethiopia
#Shebelle
ሸበሌ የምትሰኝ የኢትዮጵያ መርከብ ከ11 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ስኳርና ሩዝ ይዛ በርበራ ወደብ መድረሷን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል።
መርከቧ ከህንድ ሀገር የጫነችውን ስኳርና ሩዝ ይዛ አሁን ላይ ኢትዮጵያ ድርሻ ባላት የበርበራ ወደበ እያራገፈች ነው።
በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ የኢትዮጵያ መርከቦች ወደ በርበራ ወደብ ጉዞ ሲያደርጉ ከ20 ዓመታት በኋላ ሸበሌ መርከብ ሁለተኛ ናት።
ባለፈው ሰኔ ወር መጨረሻ ከ20 ዓመታት በኋላ ጊቤ መርከብ በበርበራ ወደብ የመጀመሪያ ጉዞ አድርጋ ነበር፤ በዚህ ጉዞም 11 ሺ 200 ሜትሪክ ቶን የፍጆታ ዕቃ ለሶማሌላንድ ገበያ አጓጉዛ ነበር።
NB : በበርበራ ወደብ፤ ዲ ፒ ወርልድ 51 በመቶ፣ ሶማሌላንድ 30 በመቶ እና ኢትዮጵያ ደግሞ 19 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ከዚህ ቀደም መገለፁ ይታወሳል ።
#አልአይን_ኒውስ
@tikvahethiopia
ሸበሌ የምትሰኝ የኢትዮጵያ መርከብ ከ11 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ስኳርና ሩዝ ይዛ በርበራ ወደብ መድረሷን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል።
መርከቧ ከህንድ ሀገር የጫነችውን ስኳርና ሩዝ ይዛ አሁን ላይ ኢትዮጵያ ድርሻ ባላት የበርበራ ወደበ እያራገፈች ነው።
በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ የኢትዮጵያ መርከቦች ወደ በርበራ ወደብ ጉዞ ሲያደርጉ ከ20 ዓመታት በኋላ ሸበሌ መርከብ ሁለተኛ ናት።
ባለፈው ሰኔ ወር መጨረሻ ከ20 ዓመታት በኋላ ጊቤ መርከብ በበርበራ ወደብ የመጀመሪያ ጉዞ አድርጋ ነበር፤ በዚህ ጉዞም 11 ሺ 200 ሜትሪክ ቶን የፍጆታ ዕቃ ለሶማሌላንድ ገበያ አጓጉዛ ነበር።
NB : በበርበራ ወደብ፤ ዲ ፒ ወርልድ 51 በመቶ፣ ሶማሌላንድ 30 በመቶ እና ኢትዮጵያ ደግሞ 19 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ከዚህ ቀደም መገለፁ ይታወሳል ።
#አልአይን_ኒውስ
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በፀጥታው ም/ቤት ስብሰባ የኢትዮጵያ ተወካይ ምን አሉ ?
በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልእክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ፤ የህወሓትን ጸብ አጫሪነት ለምክር ቤቱ ያብራሩ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግሰት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ተኩስ አቁም አውጆ መውጣቱ በአካባቢው ለሰብአዊ እንቅቃሴ እንዲሁም ሰላም እና መረጋጋትን ለማምጣት ነበር ብለዋል።
ሆኖም ግን ህወሓት ወደ ተኩስ አቁም የመምጣት ፍላጎት የላቸውም፤ ይባስ ብሎም ህጻናትን ወደ ውትድርና እያስገቡ ነው፤ ወላጆች ልጆቻውን ለውትድርና እንዲሰጡ እርዳታ እህልን እንደ ማስፈራሪያ እየተጠቀሙ ነው ብለዋል።
ህወሓት በአማራ እና በአፋር ክልሎች ላይ በከፈተው ጥቃት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀለቸውን እንዲሁም በህወሓት ተግባር ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በአማራ እና አፋር ክልሎች የሚገኙ አርሶ አደሮች የግብርና ስራ መስራ እንዳልቻሉም አስረድተዋል።
ቡድኑ የእርዳታ እህሎች እንቅስቃሴን እያስተጓጎለ መሆኑን በመጥቀስ፤ ሀገሪቱ እንዳትረጋጋ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀይሎች ጋር ጥምረት እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ግብ ሰላም ነው፤ ነገር ግን ህወሓት በኢትዮጵያና በሰላም መካከል እንቅፋት ሆኖ ቆሟል ሲሉም ተናግረዋል።
ሁሉም አካል የህወሓት ቡድን ከዚህ ተግባሩ እንዲታቀብ ጫና እንዲፈጥሩ ጥሪ ያቀረቡት አማባሳደር ታዬ ፤ ሁሉም የም/ቤቱ አባላት እውነታ ላይ የተመሰረተ መረጃ ብቻ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በልዩነት ውስጥ አንደነትን መፍጠር የቻለች ሀገር ነች፤ አሁን በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው ለውጥም መድሎን ሳይሆን አንድነትን ማጠናከር ላይ የሚሰራ ነው ብለዋል።
#አልአይን
@tikvahethiopia
በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልእክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ፤ የህወሓትን ጸብ አጫሪነት ለምክር ቤቱ ያብራሩ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግሰት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ተኩስ አቁም አውጆ መውጣቱ በአካባቢው ለሰብአዊ እንቅቃሴ እንዲሁም ሰላም እና መረጋጋትን ለማምጣት ነበር ብለዋል።
ሆኖም ግን ህወሓት ወደ ተኩስ አቁም የመምጣት ፍላጎት የላቸውም፤ ይባስ ብሎም ህጻናትን ወደ ውትድርና እያስገቡ ነው፤ ወላጆች ልጆቻውን ለውትድርና እንዲሰጡ እርዳታ እህልን እንደ ማስፈራሪያ እየተጠቀሙ ነው ብለዋል።
ህወሓት በአማራ እና በአፋር ክልሎች ላይ በከፈተው ጥቃት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀለቸውን እንዲሁም በህወሓት ተግባር ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በአማራ እና አፋር ክልሎች የሚገኙ አርሶ አደሮች የግብርና ስራ መስራ እንዳልቻሉም አስረድተዋል።
ቡድኑ የእርዳታ እህሎች እንቅስቃሴን እያስተጓጎለ መሆኑን በመጥቀስ፤ ሀገሪቱ እንዳትረጋጋ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀይሎች ጋር ጥምረት እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ግብ ሰላም ነው፤ ነገር ግን ህወሓት በኢትዮጵያና በሰላም መካከል እንቅፋት ሆኖ ቆሟል ሲሉም ተናግረዋል።
ሁሉም አካል የህወሓት ቡድን ከዚህ ተግባሩ እንዲታቀብ ጫና እንዲፈጥሩ ጥሪ ያቀረቡት አማባሳደር ታዬ ፤ ሁሉም የም/ቤቱ አባላት እውነታ ላይ የተመሰረተ መረጃ ብቻ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በልዩነት ውስጥ አንደነትን መፍጠር የቻለች ሀገር ነች፤ አሁን በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው ለውጥም መድሎን ሳይሆን አንድነትን ማጠናከር ላይ የሚሰራ ነው ብለዋል።
#አልአይን
@tikvahethiopia
👍1