TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፊቼ_ጨምበላላ

የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ፡፡

ቢሮው 1 ሺህ 500 ወጣቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አሳውቋል።

የፊቼ ጨምበላላ በዓል ከሲዳማ አልፎ የአለም ቅርስ በመሆኑ በዓሉ ባህልና እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ቢሮው ገልጿል።

ለስራው መሳካት ብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተቋም ከሁሉም የፌዴራልና የሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ ሰፊ ስራ እየሰሩ መቆየታቸውን እና ተግባሩ እስከ በዓሉ መባቻ ድረስ እንደሚዘልቅ ተገልጿል።

ለሰላም መጠበቅ የህብረተሰቡ ሚና ግንባር ቀደም ቦታ እንዳለው የተግለፀ ሲሆን ማንኛውም አጠራጣሪ ነገር ከተመለከቱ በቶሎ በአቅራቢያቸው ላሉ የጸጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ፦ ደሬቴድ

@tikvahethiopia
👍3