TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፊቼ_ጨምበላላ
የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ፡፡
ቢሮው 1 ሺህ 500 ወጣቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አሳውቋል።
የፊቼ ጨምበላላ በዓል ከሲዳማ አልፎ የአለም ቅርስ በመሆኑ በዓሉ ባህልና እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ቢሮው ገልጿል።
ለስራው መሳካት ብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተቋም ከሁሉም የፌዴራልና የሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ ሰፊ ስራ እየሰሩ መቆየታቸውን እና ተግባሩ እስከ በዓሉ መባቻ ድረስ እንደሚዘልቅ ተገልጿል።
ለሰላም መጠበቅ የህብረተሰቡ ሚና ግንባር ቀደም ቦታ እንዳለው የተግለፀ ሲሆን ማንኛውም አጠራጣሪ ነገር ከተመለከቱ በቶሎ በአቅራቢያቸው ላሉ የጸጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ፦ ደሬቴድ
@tikvahethiopia
የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ፡፡
ቢሮው 1 ሺህ 500 ወጣቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አሳውቋል።
የፊቼ ጨምበላላ በዓል ከሲዳማ አልፎ የአለም ቅርስ በመሆኑ በዓሉ ባህልና እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ቢሮው ገልጿል።
ለስራው መሳካት ብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተቋም ከሁሉም የፌዴራልና የሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ ሰፊ ስራ እየሰሩ መቆየታቸውን እና ተግባሩ እስከ በዓሉ መባቻ ድረስ እንደሚዘልቅ ተገልጿል።
ለሰላም መጠበቅ የህብረተሰቡ ሚና ግንባር ቀደም ቦታ እንዳለው የተግለፀ ሲሆን ማንኛውም አጠራጣሪ ነገር ከተመለከቱ በቶሎ በአቅራቢያቸው ላሉ የጸጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ፦ ደሬቴድ
@tikvahethiopia
👍3