#IFTAR
ዛሬ በደሴ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ይካሄዳል።
ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ ይገኛሉ።
ከደሴ ከተማ ኮሚኬሽን ቢሮ ባገኘነው መረጃ ዛሬ አርብ የሚካሄደው ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት እንደ አምናው " ኑ በጋራ እናፍጥር" በሚል ሲሆን ለደሴ ከተማ የክርስትና እምነት የተከታዮችም " ኑ በጋራ እናፍጥር " ውብ የሆነውን የወሎን እሴት እናስቀጥል የሚል ጥሪ ቀርቧል።
በሌላ መረጃ ነገ ቅዳሜ ረመዳን 15 (ሚያዚያ 8) በድሬዳዋ ከተማ " የአብሮነት ኢፍጣር በድሬዳዋ " በሚል በምድር ባቡር ለገሃር አደባባይ ይካሄዳል፤ በዕለቱ በአብሮነት ከማፍጠር ባለፈ የቁርዓን እጥረት ላለባቸው ከተሞች ቁርዓን የሚሰበሰብ ሲሆን እስከ 1000 ቁርዓን ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተጨማሪ የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 9 በኮምቦልቻ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት መዘጋጀቱ ተሰምቷል።
እንዲሁም በሀረር ሁለተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር ሚያዚያ 9 ከራስ ሆቴል እስከ ጁምዓ መስጂድ ድረስ ይካሄዳል ተብሏል።
በሌሎችም የሀገራችን ከተሞች ላይ ተመሳሳይ ስነ ሥዓቶችን ተከታትለን እናሳውቃለን።
ፎቶ ፦ ደሴ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ዛሬ በደሴ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ይካሄዳል።
ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ ይገኛሉ።
ከደሴ ከተማ ኮሚኬሽን ቢሮ ባገኘነው መረጃ ዛሬ አርብ የሚካሄደው ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት እንደ አምናው " ኑ በጋራ እናፍጥር" በሚል ሲሆን ለደሴ ከተማ የክርስትና እምነት የተከታዮችም " ኑ በጋራ እናፍጥር " ውብ የሆነውን የወሎን እሴት እናስቀጥል የሚል ጥሪ ቀርቧል።
በሌላ መረጃ ነገ ቅዳሜ ረመዳን 15 (ሚያዚያ 8) በድሬዳዋ ከተማ " የአብሮነት ኢፍጣር በድሬዳዋ " በሚል በምድር ባቡር ለገሃር አደባባይ ይካሄዳል፤ በዕለቱ በአብሮነት ከማፍጠር ባለፈ የቁርዓን እጥረት ላለባቸው ከተሞች ቁርዓን የሚሰበሰብ ሲሆን እስከ 1000 ቁርዓን ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተጨማሪ የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 9 በኮምቦልቻ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት መዘጋጀቱ ተሰምቷል።
እንዲሁም በሀረር ሁለተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር ሚያዚያ 9 ከራስ ሆቴል እስከ ጁምዓ መስጂድ ድረስ ይካሄዳል ተብሏል።
በሌሎችም የሀገራችን ከተሞች ላይ ተመሳሳይ ስነ ሥዓቶችን ተከታትለን እናሳውቃለን።
ፎቶ ፦ ደሴ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
👍632❤83👎66👏26🥰24😱6😢4
TIKVAH-ETHIOPIA
#IFTAR ዛሬ በደሴ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ይካሄዳል። ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ ይገኛሉ። ከደሴ ከተማ ኮሚኬሽን ቢሮ ባገኘነው መረጃ ዛሬ አርብ የሚካሄደው ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት እንደ አምናው " ኑ በጋራ እናፍጥር" በሚል ሲሆን ለደሴ ከተማ የክርስትና እምነት የተከታዮችም " ኑ በጋራ እናፍጥር " ውብ የሆነውን የወሎን እሴት እናስቀጥል የሚል ጥሪ ቀርቧል። በሌላ መረጃ ነገ ቅዳሜ ረመዳን…
#IFTAR
በደሴ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሄደ።
በደሴ ከተማ ዛሬ ሁለተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጧር ስነስርዓት " ኑ በጋራ እናፍጥር" በሚል ተካሂዷል።
የኢፍጣር ስነስርዓቱ ከ " ፒያሳ እስከ መናኸሪያ " ባለው ጎዳና ላይ የተካሄደ ሲሆን እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የደሴ ከተማ ነዋሪ ታድሟል።
በሌላ በኩል ደሴ የረመዳንን በዓል አስመልክቶ " ከኢድ እስከ ኢድ " በተሰኘው መርሃ ግብር ደሴ የሚገቡ እንግዶችን ለማስተናገድ እየተዘጋጀች ትገኛለች።
ፎቶ፦ ሶሻል ሚዲያ የተሰባሰበ
@tikvahethiopia
በደሴ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሄደ።
በደሴ ከተማ ዛሬ ሁለተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጧር ስነስርዓት " ኑ በጋራ እናፍጥር" በሚል ተካሂዷል።
የኢፍጣር ስነስርዓቱ ከ " ፒያሳ እስከ መናኸሪያ " ባለው ጎዳና ላይ የተካሄደ ሲሆን እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የደሴ ከተማ ነዋሪ ታድሟል።
በሌላ በኩል ደሴ የረመዳንን በዓል አስመልክቶ " ከኢድ እስከ ኢድ " በተሰኘው መርሃ ግብር ደሴ የሚገቡ እንግዶችን ለማስተናገድ እየተዘጋጀች ትገኛለች።
ፎቶ፦ ሶሻል ሚዲያ የተሰባሰበ
@tikvahethiopia
👍939❤163👎86👏28🥰18😱15😢2