TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ድርድርን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ ? ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦ " እስካሁን የተደረገ ድርድር የለም፤ እስከዚህ ደቂቃ ድረስ ፤ ስለድርድር ብዙ ሲወራ ሰማለሁ ግን እስካሁን ድርድር አላደረግንም፤ አላደረግንም ማለት እስከነአካቴው ድርድር የሚባል ነገር አይኖርም ማለት አይደለም። ድርድር ፣ ውይይት ማለት ችግር ተወግዷል ማለት ሳይሆን ችግር ለማስወገድ አማራጭ Alternative መንገድ አለው…
#ተጨማሪ

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ ድርድር የተናገሩት ፦

" ... አንድ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በአንድ ወቅት ያሉትን ማስታወስ ፈልጋለሁ፤ እኚህ ፕሬዜዳንይ እስራኤል እየተዋጉ ከሀማሶች ጋር ከሂዝቦላህ ጋር ይደራደራሉ።

በነገራችን ላይ TPLF ከኦነግ ጋር ይደራደር ነበር፣ ደርግ ከሻዕቢያ እና TPLF ጋር ይደራደር ነበር ድርድር ማለት እርቅ ማለት አይደለም። ድርድር ውስጥ ብዙ የሚገኙ ነገሮች አሉ። ከምሳሌ ... ምሳሌው ይቅርብኝ ግን አሉ ጥቅሞች።

እናም እኚህ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በጦርነት ጊዜ ምንም የሰላም ጫላንጭል እንደሌለ ሰላም ተስፋ እንደሌለው አስበን ጨክነን እንዋጋለን ፤ በድርድር ጊዜ ተጋጭተን እንደማናውቅ ጦርነት የሚባል እንዳልነበር በሰከነ መንፈስ እንደራደራለን ሁለቱንም የምናደርገው ለእስራኤል ጥቅም ነው ብለዋል።

እኛ በውጊያው ጊዜ የነበረን አቋም እና ሂደት ለምክር ቤት መግለፅ አይጠበቅብኝም አቋማችን ግልፅ ነው። በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ምንም የማንደራደር መሆኑ ግልፅ ነው።

አሁንም የምናደርገው የዛ ተገላቢጦሽ ሆኖ መታየት አለበት። ታስታውሳላችሁ በዝግ ስንወያይ ኢትዮጵያን አፍርሰው እነዚህ ሰዎች አዲስ አበባ አይገቡም ብያቹ ነበር በቲቪ አልተላለፈም ያ ውይይት ነበራችሁ ብዙዎቻችሁ ያኔ የተወያየነው ነገር ነው ተፈፅሞ ያየነው።

አሁንም #በድርድር የሚባል ነገር ካለ በዛው sprint ማየት ጥሩ ነው። የሰላም አማራጭ ካለ ፤ TPLF ቀልብ ከገዛ በጦርነት እንደማያዋጣው እንደማያሸንፍ ከተገነዘበ እኛ በደስታ ነው የምናየው። "

@tikvahethiopia
👍802👎50237🥰27😱14👏9😢9
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba📍 በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ፤ የቦሌ ክ/ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ሃላፊ በህገ ወጥ ንግድ ምክንያት የታሽገን የንግድ ቤት እከፍትልሃለሁ በሚል 100 ሺ ብር #ጉቦ ሲቀበል እጅ ከፍንጅ መያዙን የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ የንግድ ፅ/ቤት ሃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ ታሽጎ የነበረን የንግድ ቤት በህገ ወጥ መንገድ ለመክፈት ተስማምቶ…
#ተጨማሪ

የቦሌ ክ/ ከተማ ንግድ ቢሮ ኃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ 100 ሺህ ብር ጉቦውን የተቀበሉት ታሽጎ የነበረውን " አቤኔዘር የተሽከርካሪ እጥበት አገልግሎት ድርጅት " ን አስከፍታለሁ ፤ የንግድ ፈቃዱንም እንዲታደስ አደርጋለሁ በማለት ነው።

የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳለው ከሆነ፤ የድርጅቱ ባለንብረት በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ታሽጎ የነበረው ድርጅታቸው እንዲከፈትና ንግድ ፈቃድ እንዲታደስላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ መነሻ በማድረግ የስራ ኃላፊው 100,000 ብር ጉቦ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በኃላም 22 ጎላጎል ህንጻ በሚገኘው ካፌ ውስጥ ብሩን ሲቀበሉ #እጅ_ከፍንጅ ተይዘዋል ፤ አሁን ላይም ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።

#AMN

@tikvahethiopia
👍1.05K👎141👏73😢35🥰33😱3318