#DireDawa
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ወደ ትግል ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል።
ከንቲባው ዛሬ አመሻሹን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፥ " ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት ከእኛ ይጠበቃልና፤ እኔም ከሌሎች ወንድሞቼ ጋር ወደ ትግሉ ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ። በግንባር ተገኝተን ያዘጋጀነውን ስንቅ እናቀብላለን፤ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ጀግናው ሠራዊታችንን በወኔ እናበረታታለን " ብለዋል።
የአስተዳደሩ የፀጥታ ኃይሎችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፤ ከመቼውም ጊዜ በላይ የድሬዳዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ፤ የልማትና አስተዳደራዊ ሥራዎችን በሙሉ አቅማቸው ለማከናወን ተዘጋጅተዋል ሲሉም አሳውቀዋል።
አቶ ከድር ጁሀር ፥ " መላው ነዋሪዎች አካባቢያችሁን በመጠበቅ፤ ሠራዊቱን በመደገፍና፤ ወደ ግንባር በመዝመት፤ እንዲሁም በፀሎት ከጎናችን እንድትሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ። ያለጥርጥር ኢትዮጵያ ታሸንፋለች " ሲሉ ነው በተረጋገጠ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት።
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደግንባር ዘምተው ሰራዊቱን እንደሚመሩ ካሳወቁ በኃላ የተለያዩ ባለስልጣናት ፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ታዋቂ የስፖርት ሰዎች ጨምሮ ሌሎችም ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ እገለፁ መሆናቸው ይታወቃል።
#Teddy
@tikvahethiopia
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ወደ ትግል ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል።
ከንቲባው ዛሬ አመሻሹን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፥ " ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት ከእኛ ይጠበቃልና፤ እኔም ከሌሎች ወንድሞቼ ጋር ወደ ትግሉ ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ። በግንባር ተገኝተን ያዘጋጀነውን ስንቅ እናቀብላለን፤ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ጀግናው ሠራዊታችንን በወኔ እናበረታታለን " ብለዋል።
የአስተዳደሩ የፀጥታ ኃይሎችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፤ ከመቼውም ጊዜ በላይ የድሬዳዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ፤ የልማትና አስተዳደራዊ ሥራዎችን በሙሉ አቅማቸው ለማከናወን ተዘጋጅተዋል ሲሉም አሳውቀዋል።
አቶ ከድር ጁሀር ፥ " መላው ነዋሪዎች አካባቢያችሁን በመጠበቅ፤ ሠራዊቱን በመደገፍና፤ ወደ ግንባር በመዝመት፤ እንዲሁም በፀሎት ከጎናችን እንድትሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ። ያለጥርጥር ኢትዮጵያ ታሸንፋለች " ሲሉ ነው በተረጋገጠ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት።
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደግንባር ዘምተው ሰራዊቱን እንደሚመሩ ካሳወቁ በኃላ የተለያዩ ባለስልጣናት ፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ታዋቂ የስፖርት ሰዎች ጨምሮ ሌሎችም ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ እገለፁ መሆናቸው ይታወቃል።
#Teddy
@tikvahethiopia
👍3
#DireDawa
በድሬዳዋ በእርሻ ማሳ ውስጥ አደገኛ እፅ ተከለው የተገኙት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰማ።
የድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ አደገኛው የካናቢስ እጽ በእርሻ ማሳቻው ላይ ተክለው የተገኙ 2 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አሳውቋል።
እጹ ሊያዝ የቻለው በድሬዳዋ ከተማ ቀበሌ 08 ገንደ- ገበሬ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ተጠርጣሪ ግለሰብ በእርሻ ማሳ ውስጥ የተተከሉትን አደገኛ እፅ በመኮትኮት ላይ እንዳለ መሆኑ ተገልጿል።
ፖሊስ ወደ ቦታው የደረሰው በአካባቢው ላይ ሌላ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞ ሲሆን የአካባቢው ሚሊሻዎች ግለሰቡ እያደረገ ያለውን ህገ-ወጥ ተግባር ተመልክተው ለፖሊስ ባደረሱት ጥቆማ መሰረት ሁለት ተጠርጣሪ ግለሰቦች ከተከሉት በርካታ እጽ ጋር በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ግለሰቦች ከዚህ ቀደም በከተማው ውስጥ ይሄንኑ አደገኛ እጽ የመሸጥ ስራ ከምትሰራ ሌላ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር ግንኙነት በማድረግ ግለሰቧ አደገኛ የካናቢስ እጽ ስትሸጥ ተገኝታ ምርመራ ተጣርቶ ውሳኔ ማግኘቷን ፖሊስ ገልጿል።
በድሬዳዋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣውን አደገኛ የካናቢስ እጽ ዝውውርን ለመግታት ሰፊ ስራ እየሰራ መሆኑ ያሳወቀው ፖሊስ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል እየጎዳ የሚገኘውን አደገኛ እጽ ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፦ ድሬ ፖሊስ
@tikvahethiopia
በድሬዳዋ በእርሻ ማሳ ውስጥ አደገኛ እፅ ተከለው የተገኙት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰማ።
የድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ አደገኛው የካናቢስ እጽ በእርሻ ማሳቻው ላይ ተክለው የተገኙ 2 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አሳውቋል።
እጹ ሊያዝ የቻለው በድሬዳዋ ከተማ ቀበሌ 08 ገንደ- ገበሬ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ተጠርጣሪ ግለሰብ በእርሻ ማሳ ውስጥ የተተከሉትን አደገኛ እፅ በመኮትኮት ላይ እንዳለ መሆኑ ተገልጿል።
ፖሊስ ወደ ቦታው የደረሰው በአካባቢው ላይ ሌላ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞ ሲሆን የአካባቢው ሚሊሻዎች ግለሰቡ እያደረገ ያለውን ህገ-ወጥ ተግባር ተመልክተው ለፖሊስ ባደረሱት ጥቆማ መሰረት ሁለት ተጠርጣሪ ግለሰቦች ከተከሉት በርካታ እጽ ጋር በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ግለሰቦች ከዚህ ቀደም በከተማው ውስጥ ይሄንኑ አደገኛ እጽ የመሸጥ ስራ ከምትሰራ ሌላ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር ግንኙነት በማድረግ ግለሰቧ አደገኛ የካናቢስ እጽ ስትሸጥ ተገኝታ ምርመራ ተጣርቶ ውሳኔ ማግኘቷን ፖሊስ ገልጿል።
በድሬዳዋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣውን አደገኛ የካናቢስ እጽ ዝውውርን ለመግታት ሰፊ ስራ እየሰራ መሆኑ ያሳወቀው ፖሊስ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል እየጎዳ የሚገኘውን አደገኛ እጽ ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፦ ድሬ ፖሊስ
@tikvahethiopia
👍2