TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Sidama

ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ።

የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል።

በዚህ መሰረት ፦

- ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ከጎንና ጎን ያለበሱትን ሸራ በማንሳትና ሶስት ሰው ብቻ በመጫን እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት ፣ የህዝብ ትራንስፖርትና ታክሲዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።

- መታወቂያን በተመለከተ ፦ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ሀላፊዎች መታወቂያ መስጠት የማይችሉና ማንነቱን የሚገልፅ መረጃ በመያዝ ግለሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ጊዜያዊ መታወቂያ ማግኘት ይችላሉ።

- ከጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘ፦ ከዚህ ቀደም ያስመዘገበም ያላስመዘገበም ከነገ ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያው በሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ማስመዝገብና የፈቃድ ወረቀት መያዝ ይኖርበታል።

NB: ይህን ያላደረገና ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ ይዞ የተገኘ ማንኛውም አካል እንደ ወንጀለኛ የሚጠየቅ ይሆናል።

- ፋብሪካዎች፣ ኢንደስትሪ ፖርኮች፣ ሪዞርቶችና አለም አቀፍ ሆቴሎች የሰራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከፖሊስ ኮሚሽኑ ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ።

- ከሲዳማ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ወደ ክልሉ የሚገቡ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መግባት አይችሉም። በእግረኞችና የቤት መኪኖች ላይ የሰዓት ገደብ ባይጣልም መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

@tikvahethiopia
👍3
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sidama ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ። የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል። በዚህ መሰረት ፦ - ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ…
#Sidama

የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ ከዛሬ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የጦር መሳሪያ ፈቃድ መስጠት የተከለከለ መሆኑን አስታውቋል።

ቀደም ሲል በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተጣሉ እገዳዎችም መነሳታቸውን ተገልጿል።

ከዛሬ ጀምሮ በክልሉ የጦር መሳሪያ ፈቃድ መስጠት መታገዱን የተገለፀ ሲሆን ክልከላውን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ማስጠንቀቂያ ተላልፏል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ገደብ የተጣለባቸው የህዝብ ትራንስፖርት፣ የከተማ ታክሲና ባጃጅ አገልግሎቶች ላይ ክልከላው ሙሉ በሙሉ ተነስቷል።

ነገር ግን ባጃጅ አሽከርካሪዎች በሁለቱም በኩል ባጃጅ በሸራ ሳይሸፈን ማሽከርከር እንዳለባቸው ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በሌላ በኩል የሞተር ሳይክል የእንቅስቃሴ ገደብ ሙሉ በሙሉ አለመነሳቱ የተገለፀ ሲሆን በቀድሞ እገዳ ላይ ማሻሻያ ተደርጎ ከማለዳው 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት ድረስ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር እንደሚቻል ተገልጿል።

Credit : SRTA

@tikvahethiopia
2👍1