#Sidama
ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ።
የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚህ መሰረት ፦
- ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ከጎንና ጎን ያለበሱትን ሸራ በማንሳትና ሶስት ሰው ብቻ በመጫን እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት ፣ የህዝብ ትራንስፖርትና ታክሲዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።
- መታወቂያን በተመለከተ ፦ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ሀላፊዎች መታወቂያ መስጠት የማይችሉና ማንነቱን የሚገልፅ መረጃ በመያዝ ግለሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ጊዜያዊ መታወቂያ ማግኘት ይችላሉ።
- ከጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘ፦ ከዚህ ቀደም ያስመዘገበም ያላስመዘገበም ከነገ ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያው በሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ማስመዝገብና የፈቃድ ወረቀት መያዝ ይኖርበታል።
NB: ይህን ያላደረገና ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ ይዞ የተገኘ ማንኛውም አካል እንደ ወንጀለኛ የሚጠየቅ ይሆናል።
- ፋብሪካዎች፣ ኢንደስትሪ ፖርኮች፣ ሪዞርቶችና አለም አቀፍ ሆቴሎች የሰራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከፖሊስ ኮሚሽኑ ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ።
- ከሲዳማ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ወደ ክልሉ የሚገቡ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መግባት አይችሉም። በእግረኞችና የቤት መኪኖች ላይ የሰዓት ገደብ ባይጣልም መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
@tikvahethiopia
ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ።
የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚህ መሰረት ፦
- ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ከጎንና ጎን ያለበሱትን ሸራ በማንሳትና ሶስት ሰው ብቻ በመጫን እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት ፣ የህዝብ ትራንስፖርትና ታክሲዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።
- መታወቂያን በተመለከተ ፦ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ሀላፊዎች መታወቂያ መስጠት የማይችሉና ማንነቱን የሚገልፅ መረጃ በመያዝ ግለሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ጊዜያዊ መታወቂያ ማግኘት ይችላሉ።
- ከጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘ፦ ከዚህ ቀደም ያስመዘገበም ያላስመዘገበም ከነገ ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያው በሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ማስመዝገብና የፈቃድ ወረቀት መያዝ ይኖርበታል።
NB: ይህን ያላደረገና ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ ይዞ የተገኘ ማንኛውም አካል እንደ ወንጀለኛ የሚጠየቅ ይሆናል።
- ፋብሪካዎች፣ ኢንደስትሪ ፖርኮች፣ ሪዞርቶችና አለም አቀፍ ሆቴሎች የሰራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከፖሊስ ኮሚሽኑ ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ።
- ከሲዳማ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ወደ ክልሉ የሚገቡ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መግባት አይችሉም። በእግረኞችና የቤት መኪኖች ላይ የሰዓት ገደብ ባይጣልም መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
@tikvahethiopia
👍3