#update ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ⬇️
የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር #ወርቅነህ_ገበየሁ በ73ኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ለአካባቢው ሰላም እና ዘላቂ ልማት ተግታ የምትሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ እንደ ተመድ መስራች አባል ሀገር ለባለብዙ ወገን መድረክ ትኩረት በመስጠት የተ.መ.ድ መርህ እንዲከበር እንዲሁም ተግዳሮቶች እና ስጋቶች እንዲወገዱ በጋራ ትሰራለች ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የተካሄደው ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ለሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ክስተት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እንዲሁም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ተሰፋው እንዲፈነጥቅ ያደረገ መሆኑንም ዶ/ር ወርቅነህ አውስተዋል፡፡
የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ የአገር ኢኮኖሚ በአግባቡ ለማስተዳደር እንዲቻል፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ የብዙሃኑ ተሳትፎ እንዲረጋገጥ እንዲሁም ዴሞክራሲ እንዲያብብ ለማድረግ መንግስት በስፋት እና በጥልቀት እየሰራ መሆኑን ሚኒስትሩ
ተናግረዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚመራው መንግስት በሁሉም አቅጣጫ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እና እንደ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ መልካም አስተዳደር ያሉትን የእድግት ማነቆዎች ለመቅረፍ በርካታ ተግባራት እየከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በቀጠናው የሰላም አየር እንዲነፍስ ያበረከተቸውን አስተዋጽኦም አብራርተዋል።
ለ20 አመታት ያክል በግጭት ላይ የነበሩት ኢትዮጵያና ኤርትራ አዲስ የግንኙነት ምዕራፍ መክፈታቸው፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ እንዲሁም #ጅቡቲ እና #ኤርትራ ችግሮቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ የተደረገው ጥረት ከቀጠናው አልፎ ለአፍሪካ ሰላም ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ
መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡
©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር #ወርቅነህ_ገበየሁ በ73ኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ለአካባቢው ሰላም እና ዘላቂ ልማት ተግታ የምትሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ እንደ ተመድ መስራች አባል ሀገር ለባለብዙ ወገን መድረክ ትኩረት በመስጠት የተ.መ.ድ መርህ እንዲከበር እንዲሁም ተግዳሮቶች እና ስጋቶች እንዲወገዱ በጋራ ትሰራለች ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የተካሄደው ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ለሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ክስተት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እንዲሁም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ተሰፋው እንዲፈነጥቅ ያደረገ መሆኑንም ዶ/ር ወርቅነህ አውስተዋል፡፡
የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ የአገር ኢኮኖሚ በአግባቡ ለማስተዳደር እንዲቻል፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ የብዙሃኑ ተሳትፎ እንዲረጋገጥ እንዲሁም ዴሞክራሲ እንዲያብብ ለማድረግ መንግስት በስፋት እና በጥልቀት እየሰራ መሆኑን ሚኒስትሩ
ተናግረዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚመራው መንግስት በሁሉም አቅጣጫ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እና እንደ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ መልካም አስተዳደር ያሉትን የእድግት ማነቆዎች ለመቅረፍ በርካታ ተግባራት እየከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በቀጠናው የሰላም አየር እንዲነፍስ ያበረከተቸውን አስተዋጽኦም አብራርተዋል።
ለ20 አመታት ያክል በግጭት ላይ የነበሩት ኢትዮጵያና ኤርትራ አዲስ የግንኙነት ምዕራፍ መክፈታቸው፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ እንዲሁም #ጅቡቲ እና #ኤርትራ ችግሮቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ የተደረገው ጥረት ከቀጠናው አልፎ ለአፍሪካ ሰላም ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ
መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡
©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
የተዘጋው መንገድ ሙሉ በሙሉ አልተከፈተም‼️
በተቃውሞ ሳቢያ የተዘጋው የአዲስ አበባ፤ አዋሽ ጅቡቲ መንገድ ዛሬም ሙሉ በሙሉ #አልተከፈተም። ወደ #ጅቡቲ የሚያመራው እና የኢትዮጵያ ገቢ እና ወጪ ንግድ የደም ሥር እንደሆነ የሚነገርለት የመኪና መንገድ አዋሽ ሰባት ከተማ ላይ ዛሬም ለተሽከርካሪዎች ዝግ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪ ለDW አረጋግጠዋል።
ተቃዋሚዎች ከትናንት ጀምሮ ዋናው መንገድ ከሚያልፍባት የአዋሽ ከተማ መውጪ እና መግቢያዎች እንደዘጉ መሆናቸውን የዐይን እማኙ ተናግረዋል።
በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት የአዋሽ ነዋሪ "መንገዱ አልተከፈተም፤ ምንም የሚንቀሳቀስ ነገር የለም" ብለዋል።
በሎጊያ አካባቢ የሚገኘው የመንገዱ ክፍል ግን በዛሬው ዕለት ተከፍቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን አንድ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ተናግረዋል። ትናንት መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት መንገድ ላይ ማደራቸውን ለDW የገለጹት አሽከርካሪ ዛሬ ወደ ሎጊያ ከተማ ለመግባት መቻላቸውን ገልጸዋል። ተቃዋሚዎች ከክልሉ መንግሥት ጋር በመነጋገር ላይ ስለመሆኑ መረጃ እንደደረሳቸው የገለጹት የከባድ መኪና አሽከርካሪ "ሕዝቡ ለሰባት ቀን ጊዜ ሰጥቶ አሁን መኪና መንቀሳቀስ ጀምሯል። በሰባት ቀናት ውስጥ ጥያቄያችን ካልተመለሰ #አሁንም_እንዘጋለን ብለዋል" ሲሉ ኹኔታውን አስረድተዋል።
በአዋሽ ሰባት የሚኖሩት ነጋዴ ግን የአካባቢውን የንግድ እንቅስቃሴ ክፍኛ ያስተጓጎለው የመንገድ መዘጋት "እስከ ነገው ዕለት ይቀጥላል" የሚል መረጃ ደርሷቸዋል። "ሶስት ቀን እያሉ ነው። ነገንም ይጨምራል መሰለኝ" ያሉት የአዋሽ ሰባት ነዋሪ ከመንግሥት መፍትሔ ካልተገኘ ሊከፈት እንደማችል በተቃውሞው የተካፈሉ ሲዝቱ መስማታቸውን ለDW አረጋግጠዋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በተቃውሞ ሳቢያ የተዘጋው የአዲስ አበባ፤ አዋሽ ጅቡቲ መንገድ ዛሬም ሙሉ በሙሉ #አልተከፈተም። ወደ #ጅቡቲ የሚያመራው እና የኢትዮጵያ ገቢ እና ወጪ ንግድ የደም ሥር እንደሆነ የሚነገርለት የመኪና መንገድ አዋሽ ሰባት ከተማ ላይ ዛሬም ለተሽከርካሪዎች ዝግ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪ ለDW አረጋግጠዋል።
ተቃዋሚዎች ከትናንት ጀምሮ ዋናው መንገድ ከሚያልፍባት የአዋሽ ከተማ መውጪ እና መግቢያዎች እንደዘጉ መሆናቸውን የዐይን እማኙ ተናግረዋል።
በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት የአዋሽ ነዋሪ "መንገዱ አልተከፈተም፤ ምንም የሚንቀሳቀስ ነገር የለም" ብለዋል።
በሎጊያ አካባቢ የሚገኘው የመንገዱ ክፍል ግን በዛሬው ዕለት ተከፍቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን አንድ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ተናግረዋል። ትናንት መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት መንገድ ላይ ማደራቸውን ለDW የገለጹት አሽከርካሪ ዛሬ ወደ ሎጊያ ከተማ ለመግባት መቻላቸውን ገልጸዋል። ተቃዋሚዎች ከክልሉ መንግሥት ጋር በመነጋገር ላይ ስለመሆኑ መረጃ እንደደረሳቸው የገለጹት የከባድ መኪና አሽከርካሪ "ሕዝቡ ለሰባት ቀን ጊዜ ሰጥቶ አሁን መኪና መንቀሳቀስ ጀምሯል። በሰባት ቀናት ውስጥ ጥያቄያችን ካልተመለሰ #አሁንም_እንዘጋለን ብለዋል" ሲሉ ኹኔታውን አስረድተዋል።
በአዋሽ ሰባት የሚኖሩት ነጋዴ ግን የአካባቢውን የንግድ እንቅስቃሴ ክፍኛ ያስተጓጎለው የመንገድ መዘጋት "እስከ ነገው ዕለት ይቀጥላል" የሚል መረጃ ደርሷቸዋል። "ሶስት ቀን እያሉ ነው። ነገንም ይጨምራል መሰለኝ" ያሉት የአዋሽ ሰባት ነዋሪ ከመንግሥት መፍትሔ ካልተገኘ ሊከፈት እንደማችል በተቃውሞው የተካፈሉ ሲዝቱ መስማታቸውን ለDW አረጋግጠዋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፈጣሪ ያውቃል⁉️
በረሐ እና ባሕር አቋርጠው ወደ ሳዑዲ አረቢያ የሚተሙት ኢትዮጵያውያን በየመን ጦርነት እንዳለ እንኳ አያውቁም። አንድ ወደ #ጅቡቲ የተሰደደ #የመናዊ በመንገድ ያገኟቸውን ኢትዮጵያውያን «ወዴት ነው የምትሔዱት? በመንገዳችሁ ጦርነት አለ ስንላቸው ፈጣሪ ያውቃል» የሚል መልስ ሰጡን ሲል ለኢኤንኤን ተናግሯል።
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ድረ-ገፅ እደሚጠቁመው በየመን የርስ በርስ #ጦርነት፦
•5,900+ ሰላማዊ ሰዎች #ተገድለዋል
•9,400+ ሰላማዊ ሰዎች #ቆስለዋል
•3 ሚሊዮን ከመኖሪያ ቀያቸው #ተፈናቅለዋል
•22.2 ሚሊዮን ሕይወታቸውን ለማቆየት የለት ደራሽ ዕርዳታ #ጥገኛ ናቸው
•2.5 ሚሊዮን ሕፃናት ከትምህርት ገበታ እርቀዋል፤ ቢሆንም #ኢትዮጵያውያኑ ፈጣሪ ያውቃል እያሉ መንገድ ላይ ናቸው።
Via Eshet Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በረሐ እና ባሕር አቋርጠው ወደ ሳዑዲ አረቢያ የሚተሙት ኢትዮጵያውያን በየመን ጦርነት እንዳለ እንኳ አያውቁም። አንድ ወደ #ጅቡቲ የተሰደደ #የመናዊ በመንገድ ያገኟቸውን ኢትዮጵያውያን «ወዴት ነው የምትሔዱት? በመንገዳችሁ ጦርነት አለ ስንላቸው ፈጣሪ ያውቃል» የሚል መልስ ሰጡን ሲል ለኢኤንኤን ተናግሯል።
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ድረ-ገፅ እደሚጠቁመው በየመን የርስ በርስ #ጦርነት፦
•5,900+ ሰላማዊ ሰዎች #ተገድለዋል
•9,400+ ሰላማዊ ሰዎች #ቆስለዋል
•3 ሚሊዮን ከመኖሪያ ቀያቸው #ተፈናቅለዋል
•22.2 ሚሊዮን ሕይወታቸውን ለማቆየት የለት ደራሽ ዕርዳታ #ጥገኛ ናቸው
•2.5 ሚሊዮን ሕፃናት ከትምህርት ገበታ እርቀዋል፤ ቢሆንም #ኢትዮጵያውያኑ ፈጣሪ ያውቃል እያሉ መንገድ ላይ ናቸው።
Via Eshet Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
😭1
#Attention
ከአፋር የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች!
"...ግጭቱ አሁን መልክ እየቀየረ እስከ #ጅቡቲ ደረስ እየዘለቀ በመሆኑ ከመንግስት በኩል አስቸኳይ መፍትሔ ካልተሰጠው የቀጠናው ሰላም ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን መታወቅ አለበት።"
ለማዕከላዊ መንግስት ይድረስ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአፋር የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች!
"...ግጭቱ አሁን መልክ እየቀየረ እስከ #ጅቡቲ ደረስ እየዘለቀ በመሆኑ ከመንግስት በኩል አስቸኳይ መፍትሔ ካልተሰጠው የቀጠናው ሰላም ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን መታወቅ አለበት።"
ለማዕከላዊ መንግስት ይድረስ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia