TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UNSC

ዛሬ የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ይመክራል።

ስብሰባው ላይ ለመካፈል የኢትዮጵያ ዉኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ ወደ ኒውዮርክ ማቅናታቸውን አል አል ዐይን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ የፀጥታው ምክር ቤት ኢትዮጵያ ፣ ግብፅ እና ሱዳን በገጠሙት የግድቡ ዉዝግብ ላይ ለመነጋገር በሚያደርገው ስብሰባ ላይ #ኢትዮጵያን ይወክላሉ፡፡

በስብሰባው ላይም የኢትዮጵያን አቋም ያንጸባርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኢትዮጵያን ከሚወክሉት ዶ/ር ኢ ር ስለሺ በቀለ በተጨማሪ በስብሰባዉ ላይ የግብፅና የሱዳን ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች የሚገኙ ይሆናል፡፡

ከሶስቱ ሀገራት ሚንስትሮች በተጨማሪ ፦
- በአፍሪቃ ቀንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዩ መልዕክተኛ፣
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአካባቢ ጥበቃ ኃላፊ
- የወቅቱ የአፍሪቃ ሕብረት ሊቀመንበር የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዲፕሎማት ለተሰብሳቢዎች ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አል ዓይን አስነብቧል።

@tikvahethiopia
👍1