TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UNHCR

UNHCR ኤርትራውያን ስደተኞችን ከትግራይ ክልል እያስወጣ ነው።

ለደይሊ ኔሽን ጋዜጣ በሰጠው ቃል ከ20,000 በላይ ኤርትራውያን ስደተኞችን ከትግራይ ክልል የማስወጣቱ ሂደት መጀመሩን አረጋግጧል።

የUNHCR ቃል አቀባይ Neven Crvenkovic "ከ20 ሺህ በላይ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ከትግራይ ክልል የማስወጣት ሂደት መጀመሩን ገልፀው ስደተኞቹ ማይ ዓይኒ እንዲሁም አዲ ሐሩሽ በተባሉት ስደተኛ መጠለያዎች ተጠልለው የቆዩ እንደሆኑ አስረድተዋል።

ኤርትራውያን ስደተኞች አሁን ላይ የሚዛወሩት በአማራ ክልል " ዳባት ወረዳ " ወደተሠሩት አዲስ ስደተኛ መጠለያዎች ነው፡፡

አዲሱ የዳባት ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ 25 ሺህ ስደተኞችን ማስተናገድ ይችላል።

#Nation

@tikvahethiopia