TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የከፋ ዞን ምክር ቤት‼️

የካፋ ዞን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ #ቦንጋ ላይ የተገነባው ብሔራዊ የቡና ሙዚዬም ሥራ እንዲጀምር ወሰነ።

የካፋ ዞን #የክልልነት ጥያቄንም በምክር ቤቱ አባላት ጸድቋል።

የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ ግርማ ወልደ ሚካዔል ለኢዜአ እንደገለጹት ጉባዔው በዛሬው ወሎ በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አስተሏልፏል ።

ጉባዔው ውሳኔ ካሳለፈባቸው አጀንዳዎች አንዱ በዞኑ ቦንጋ ከተማ ተገንብቶ ለአመታት ሥራ ያልጀመረው ሙዚዬም ወደ ሥራ እንዲገባ ወስኗል።

“ከምሁራን የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ሙዚዬሙ ወደ ሥራ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል” ብለዋል ።

የካፋ ሕዝብ የክልልነት ጥያቄ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በአባላቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሙሉ ድምጽ መፅደቁን ምክትል አፈ ጉባዔው ተናግረዋል።

ጉባኤው ነገ የዞኑን የ2010 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ ክንውን በመገምገምና በቀጣይ ዕቅድ ላይ በመወያየት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አመላክተዋል ።

እንደ ምክትል አፈ ጉባኤው ገለጻ በተለያዩ ምክንያቶች ያልጸደቀውን የዞኑን የ2011 በጀትና የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሹመትም እንደሚፀድቅ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቦንጋ

"በአሁን ሰዓት በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ያስተላለፈውን መግለጫ በመቃወም፤ መግለጫው እኛን አይወክለንም በማለት እንዲሁም ካፋ ዞን ራሱ በራሱን ያስተዳድር የክልልነት ጥያውቄው ይመለስለት "ክልላችን ካፋ ነው" በሚል ሰላማዊ ሰልፍ በመደረግ ላይ ይገኛል። የሰልፉ ተካፋዮች ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ ናቸው።"

Via #SAMI

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቦንጋ

•ሀገራዊ ለውጡ ይቅደም ብለን እንጂ ጥያቄያችን በበቂ ምክንያት ነው!!

•ከእንግዲህ ለግማሽ ቀን ስብሰባ ሁለት ቀን እንጓዝም!!

•የካፋ ህዝብ ክልል የመሆን ጥያቅም ፍትሃዊ ምላሽ እንጂ ድጋሚ ጥያት አያሻውም!!

•ክልላችን ካፋ ነው!!

•የካፋ ህዝብ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ታሪካዊ ልምድና አቅም አለው!!

በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ሰላማዊ ሰልፍ አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል። ከተለያዩ ወረዳዎችም በርካታ ሰዎች ወደ ቦንጋ እየገቡ እንደሆነ ለማውቅ ተችሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia