#FDREDefenseForce
በአሚሶም ሴክተር 6 የሚገኘው የ5ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዓመታዊ የሜዳሊያ በዓሉ አከበረ።
በፕሮግራሙ ላይ የጁባ ላንድ ምክትል ፕሬዝዳት የሆኑት አቶ መሃመድ ሰይድ ተገኝተው ነበር።
ም/ፕሬዝዳት አቶ መሃመድ በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል አልሸባብን ለማጥፋት ያደረገው የግዳጅ አፈፃፀም ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ ተናግረዋል።
አክለው ፤ ሰራዊቱ በድስፕሊኑ የታነፀ ከህዝቡ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት ያለውና በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ላሳየው ቁርጠኝነት ሜዳሊያው በክብር እንደተሰጠው ግልፀዋል።
የሴክተር 6 አዛዥ የሆኑት ብ/ጄ አበባው ሰይድ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ፣ የኬንያና የሴራሊዮን የፖሊስ ሃይል እንዲሁም የUN አጋዥ ሃይሎች ዓመቱን ሙሉ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ሰላም በማስከበር ረገድ ስመ ጥር ሃገር እንደሆነች እና በተለይ በሶማሊያ የአልሸባብን ሃይል በማጥፋት እንዲሁም የገንዘብ ምንጩን በማዳከም የሶማሊያን ሰላም በማጠናከር ትልቁን ሚና እየተወጣች መሆኑን አሳውቀዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው።
@tikvahethiopia
በአሚሶም ሴክተር 6 የሚገኘው የ5ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዓመታዊ የሜዳሊያ በዓሉ አከበረ።
በፕሮግራሙ ላይ የጁባ ላንድ ምክትል ፕሬዝዳት የሆኑት አቶ መሃመድ ሰይድ ተገኝተው ነበር።
ም/ፕሬዝዳት አቶ መሃመድ በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል አልሸባብን ለማጥፋት ያደረገው የግዳጅ አፈፃፀም ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ ተናግረዋል።
አክለው ፤ ሰራዊቱ በድስፕሊኑ የታነፀ ከህዝቡ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት ያለውና በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ላሳየው ቁርጠኝነት ሜዳሊያው በክብር እንደተሰጠው ግልፀዋል።
የሴክተር 6 አዛዥ የሆኑት ብ/ጄ አበባው ሰይድ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ፣ የኬንያና የሴራሊዮን የፖሊስ ሃይል እንዲሁም የUN አጋዥ ሃይሎች ዓመቱን ሙሉ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ሰላም በማስከበር ረገድ ስመ ጥር ሃገር እንደሆነች እና በተለይ በሶማሊያ የአልሸባብን ሃይል በማጥፋት እንዲሁም የገንዘብ ምንጩን በማዳከም የሶማሊያን ሰላም በማጠናከር ትልቁን ሚና እየተወጣች መሆኑን አሳውቀዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው።
@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce
የመተከል ዞን የተቀናጀው ግብረ ኃይል ኮማንድ ፖስት አመራሮች እና የየመስተዳድር አካላት የተካተቱበት ልዑክ ተፈናቃዮች በሚገኙበት አራት የጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በአካባቢው ተከስቶ በነበረው ግጭት ሳቢያ ከቀዬአቸው ተፈናቅለው ከነበሩ ወገኖች ጋር የጋራ ውይይት ማድረጋቸውም ተገልጿል። ውይይቱ በግዜያዊ መጠለያ ጣቢያው የሚያጋጥሙ ችግሮች እና መፍትሄዎች ላይ አተኩሮ የተካሄደ ነበር።
የመተከል ዞን የተቀናጀው ግብረ ኃይል ኮማንድ ፖስት አባል የሆኑት ብ/ል ጄኔራል አለማየሁ ወልዴ ተፈናቃዮችን ቋሚ ተፈናቃይ አድርጎ በማቆየት በግላቸው የሚጠቀሙ ሀይሎች መኖራቸውን የጠቆሙ ሲሆን የእነዚህን ሀይሎች ሴራ መረዳትና በጋራ መታገል አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለህዝቡ የሚቀርበውን የምግብ እህሎችን ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦችን በህዝቡ ተሳትፎ በመለየት ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉንም አስታውሰዋል። ይሄ ተግባር በቀጣይነት ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ ልዩ ልዩ የመመገቢያ ቁሳቆሶች እና ሰብአዊ እርዳታዎች መድረስ ከሚገባው ግዜ መዘግየቶች ማጋጠማቸውን የጠቆሙ ሲሆን አስቸኳይ መፍትሄ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
የመተከል ዞን የተቀናጀው ግብረ ኃይል ኮማንድ ፖስት አመራሮች እና የየመስተዳድር አካላት የተካተቱበት ልዑክ ተፈናቃዮች በሚገኙበት አራት የጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በአካባቢው ተከስቶ በነበረው ግጭት ሳቢያ ከቀዬአቸው ተፈናቅለው ከነበሩ ወገኖች ጋር የጋራ ውይይት ማድረጋቸውም ተገልጿል። ውይይቱ በግዜያዊ መጠለያ ጣቢያው የሚያጋጥሙ ችግሮች እና መፍትሄዎች ላይ አተኩሮ የተካሄደ ነበር።
የመተከል ዞን የተቀናጀው ግብረ ኃይል ኮማንድ ፖስት አባል የሆኑት ብ/ል ጄኔራል አለማየሁ ወልዴ ተፈናቃዮችን ቋሚ ተፈናቃይ አድርጎ በማቆየት በግላቸው የሚጠቀሙ ሀይሎች መኖራቸውን የጠቆሙ ሲሆን የእነዚህን ሀይሎች ሴራ መረዳትና በጋራ መታገል አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለህዝቡ የሚቀርበውን የምግብ እህሎችን ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦችን በህዝቡ ተሳትፎ በመለየት ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉንም አስታውሰዋል። ይሄ ተግባር በቀጣይነት ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ ልዩ ልዩ የመመገቢያ ቁሳቆሶች እና ሰብአዊ እርዳታዎች መድረስ ከሚገባው ግዜ መዘግየቶች ማጋጠማቸውን የጠቆሙ ሲሆን አስቸኳይ መፍትሄ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
👍1