TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FDREDefenseForce

በአሚሶም ሴክተር 6 የሚገኘው የ5ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዓመታዊ የሜዳሊያ በዓሉ አከበረ።

በፕሮግራሙ ላይ የጁባ ላንድ ምክትል ፕሬዝዳት የሆኑት አቶ መሃመድ ሰይድ ተገኝተው ነበር።

ም/ፕሬዝዳት አቶ መሃመድ በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል አልሸባብን ለማጥፋት ያደረገው የግዳጅ አፈፃፀም ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ ተናግረዋል።

አክለው ፤ ሰራዊቱ በድስፕሊኑ የታነፀ ከህዝቡ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት ያለውና በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ላሳየው ቁርጠኝነት ሜዳሊያው በክብር እንደተሰጠው ግልፀዋል።

የሴክተር 6 አዛዥ የሆኑት ብ/ጄ አበባው ሰይድ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ፣ የኬንያና የሴራሊዮን የፖሊስ ሃይል እንዲሁም የUN አጋዥ ሃይሎች ዓመቱን ሙሉ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ሰላም በማስከበር ረገድ ስመ ጥር ሃገር እንደሆነች እና በተለይ በሶማሊያ የአልሸባብን ሃይል በማጥፋት እንዲሁም የገንዘብ ምንጩን በማዳከም የሶማሊያን ሰላም በማጠናከር ትልቁን ሚና እየተወጣች መሆኑን አሳውቀዋል።

መረጃው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው።

@tikvahethiopia