#ማሳሰቢያ
የኳታር መንግስት ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን እና ሽብርተኝነትን በፋይናንስ መደገፍን ለመከላከል ባወጣው አዋጅ ቁጥር 20/2019 “ማንኛውም ዜጋ ወደ አገሪቱ ሲገባም ሆነ ሲወጣ ከ 50,000 በላይ የቀጠር ሪያል ካሽ እና ተመሳሳይ ዋጋ ያላቸው ውድ ጌጣ ጌጦችን ለጉምሩክ መስሪያ ቤት ማሳወቅ እንደሚገባው” ደንግጓል።
ከላይ የተጠቀሱ ንብረቶች ሳያሳውቁ ከሀገር ለመውጣት ወይም ለመግባት መሞከር ፣ የተሳሳተ መረጃ መስጠት ወይም ደግሞ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን ንብረቱን ከመወረስ አልፎ እስከ 3 ዓመት እስር ወይም ከ100,000 እስከ 500,000 የኳታር ሪያል ቅጣት እንደሚያስከትል በህጉ ተቀምጧል።
በመሆኑም በኳታር ነዋሪ የሆናችሁ የኢትዮጵያ ዜጎች ከአገሪቱ ስትወጡም ሆነ ስትገቡ የምትይዙትን ከ50,000 በላይ የሆነ የቀጠር ሪያል የገንዘብ መጠን (በኳታር ሪያል፣ በውጭ አገር ገንዘቦች፣ በቼክ እና የመሳሰሉት) እንዲሁም ከላይ ከተገለጸው የገንዘብ መጠን በላይ ዋጋ ያላቸውን ውድ ንብረቶች (ወርቅ ፣ ብር ፣ ፕላቲኒዬም፣ ዳያመንድ እና የመሳሰሉትን) በጉምሩክ ጣቢያዎች በማስመዝገብ (declare በማድረግ) ከማንኛውም ህጋዊ ርምጃ ራሳችሁን እንድትጠብቁ በዶሃ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኳታር መንግስት ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን እና ሽብርተኝነትን በፋይናንስ መደገፍን ለመከላከል ባወጣው አዋጅ ቁጥር 20/2019 “ማንኛውም ዜጋ ወደ አገሪቱ ሲገባም ሆነ ሲወጣ ከ 50,000 በላይ የቀጠር ሪያል ካሽ እና ተመሳሳይ ዋጋ ያላቸው ውድ ጌጣ ጌጦችን ለጉምሩክ መስሪያ ቤት ማሳወቅ እንደሚገባው” ደንግጓል።
ከላይ የተጠቀሱ ንብረቶች ሳያሳውቁ ከሀገር ለመውጣት ወይም ለመግባት መሞከር ፣ የተሳሳተ መረጃ መስጠት ወይም ደግሞ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን ንብረቱን ከመወረስ አልፎ እስከ 3 ዓመት እስር ወይም ከ100,000 እስከ 500,000 የኳታር ሪያል ቅጣት እንደሚያስከትል በህጉ ተቀምጧል።
በመሆኑም በኳታር ነዋሪ የሆናችሁ የኢትዮጵያ ዜጎች ከአገሪቱ ስትወጡም ሆነ ስትገቡ የምትይዙትን ከ50,000 በላይ የሆነ የቀጠር ሪያል የገንዘብ መጠን (በኳታር ሪያል፣ በውጭ አገር ገንዘቦች፣ በቼክ እና የመሳሰሉት) እንዲሁም ከላይ ከተገለጸው የገንዘብ መጠን በላይ ዋጋ ያላቸውን ውድ ንብረቶች (ወርቅ ፣ ብር ፣ ፕላቲኒዬም፣ ዳያመንድ እና የመሳሰሉትን) በጉምሩክ ጣቢያዎች በማስመዝገብ (declare በማድረግ) ከማንኛውም ህጋዊ ርምጃ ራሳችሁን እንድትጠብቁ በዶሃ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ
በጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሚካሄደው ጥገና ምክንያት የጢስ አባይ ፏፏቴ ውሃ ከነገ የካቲት 27/2013 ዓ/ም ጀምሮ መጠኑ ጨምሮ ስለሚለቀቅ ከፏፏቴው ግርጌ በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተብሏል።
#መልዕክቱን_ለሌሎች_ያድረሱ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሚካሄደው ጥገና ምክንያት የጢስ አባይ ፏፏቴ ውሃ ከነገ የካቲት 27/2013 ዓ/ም ጀምሮ መጠኑ ጨምሮ ስለሚለቀቅ ከፏፏቴው ግርጌ በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተብሏል።
#መልዕክቱን_ለሌሎች_ያድረሱ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia