TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኡጋንዳ

የውጭ ጉዳይ እና የመከላከያ ሚንስትሮች #በኡጋንዳ ከሚኖሩ #ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያዩ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ በኡጋንዳ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚንስትሮቹ ከኢትዮጵያዊያኑ ጋር የተወያዩት በሀገሪቱ እየተካሄደ ባለው ለውጥ ዙሪያ ነው ተብሏል፡፡ ውይይቱ ከ3ኛው የኢትዮ ኡጋንዳ የሚኒስትሮች ስብሰባ ጎን ለጎን የተካሄደ ነው።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ አፍሪካ እስካሁን በትንሹ 10 ኢትዮጵያውያን ሞተዋል!

በደቡብ አፍሪካ እስካሁን ከ10 የማያንሱ #ኢትዮጵያውያን በኮቪድ-19 መሞታቸውን በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ ፀሃፊ አቶ ፋኖስ ሃይሌ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ጁሃንስበርግ ፣ ሊንፖፖ፣ ማፑማላንጋ እንዲሁም ዌስተርን ኬፕ ኢትዮጵያውያን ከሞቱባቸው አካባቢዎች ይጠቀሳሉ።

አስክሬናቸውን ወደ ሀገር ቤት መላክ ስለማይፈቅድ የሁሉም ቀብር ስነስርዓት በዛው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ተፈፅሟል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia