"የትግራይ ህዝብ #ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት እንቅስቃሴ #ሊረበሽ አይገባም"--ዶክተር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል
.
.
የትግራይ ህዝብ ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ሳይረበሽ #በልማቱ ላይ ሊያተኩር እንደሚገባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ገለጹ።
ምክትል ርዕሰ-መስተዳደሩ ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ህጋዊና #ኃላፊነቱንም ለመወጣት የሚያስችል ነው።
በመሆኑም የክልሉ ህዝብ ይሄንን ተገንዝቦ ያለምንም መረበሽ የልማት ስራውን #በተረጋጋ መልኩ ማከናወን እንዳለበት አሳስበዋል።
ህዝቡ የሚያነሳው የህገ-መንግስት ይከበርልን ጥያቄ እራሱ ከማክበር የሚጀምር መሆኑንም ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር በመግለጫቸው አመልክተዋል።
የክልሉን ሰላምና ጸጥታ የማስከበርን ጉዳይም ህዝቡ በፈጠረው አደረጃጀት አንድነቱን ማስቀጠል እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት ባደረጉት የጋራ ስምምነት የሁመራ ኦምሃጀር መንገድ መከፈትም ለሁለቱ ህዝቦች ግንኙነት ጠቃሚ እንደሆነ ዶክተር ደብረጽዮን ተናግረዋል።
መንገዱ የሁለቱን ሃገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከማሳደግ ባለፈው ቀጣይ ህጋዊ መስመር ለማስያዝም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
የትግራይ ህዝብ ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ሳይረበሽ #በልማቱ ላይ ሊያተኩር እንደሚገባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ገለጹ።
ምክትል ርዕሰ-መስተዳደሩ ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ህጋዊና #ኃላፊነቱንም ለመወጣት የሚያስችል ነው።
በመሆኑም የክልሉ ህዝብ ይሄንን ተገንዝቦ ያለምንም መረበሽ የልማት ስራውን #በተረጋጋ መልኩ ማከናወን እንዳለበት አሳስበዋል።
ህዝቡ የሚያነሳው የህገ-መንግስት ይከበርልን ጥያቄ እራሱ ከማክበር የሚጀምር መሆኑንም ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር በመግለጫቸው አመልክተዋል።
የክልሉን ሰላምና ጸጥታ የማስከበርን ጉዳይም ህዝቡ በፈጠረው አደረጃጀት አንድነቱን ማስቀጠል እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት ባደረጉት የጋራ ስምምነት የሁመራ ኦምሃጀር መንገድ መከፈትም ለሁለቱ ህዝቦች ግንኙነት ጠቃሚ እንደሆነ ዶክተር ደብረጽዮን ተናግረዋል።
መንገዱ የሁለቱን ሃገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከማሳደግ ባለፈው ቀጣይ ህጋዊ መስመር ለማስያዝም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአማራ ክልል ሙሉ በሙሉ በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ እንደገለጹት፥ ከሰሞኑ በተፈጸመው ድርጊት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እጃቸው አለበት የተባሉ ተጠርጣሪዎችን የክልሉ የጸጥታ ኃይል ለህግ እያቀረበ ነው።
ድርጊቱ ከተፈጸመበት ቀን እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስም ከ300 በላይ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮሚሽነር አበረ ገልጸዋል። ግለሰቦችን ወደ ህግ ለማቅረብ በተደረገው እንቅስቃሴም ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ።
የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና ማጣራቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን የተናገሩት ኮሚሽነሩ፥ ከተያዙት መካከል ጉዳያቸው ተጣርቶ የሚለቀቁ እንደሚኖሩም አመላክተዋል።
በነባሮች እና አዲስ በሰለጠኑት የልዩ ኃይል አባላት መካከል ልዩነት እንዳለ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ክልሉ ጠንካራ የጸጥታ ኃይል እንዳይኖረው የተሰራ የፖለቲካ ሴራ እንጂ ምንም አይነት ልዩነት እንደሌለም ነው የተናገሩት።
ህጋዊ ትጥቅ ያላቸውን ግለሰቦች ትጥቅ የማስፈታት ስራ ተጀምሯል እየተባለ የሚሰራጨው ወሬ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ ታስቦ የሚናፈስና ከእውነት የራቀ አሉባልታ መሆኑንም ኮሚሽነር አበረ ተናግረዋል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ ስጋት ውስጥ እንዳይገባም መልዕክት ያስተላለፉት ኮሚሽነሩ ፥ ክልሉ ሙሉ በሙሉ #በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
Via #EPA
🗞ቀን 22/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ እንደገለጹት፥ ከሰሞኑ በተፈጸመው ድርጊት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እጃቸው አለበት የተባሉ ተጠርጣሪዎችን የክልሉ የጸጥታ ኃይል ለህግ እያቀረበ ነው።
ድርጊቱ ከተፈጸመበት ቀን እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስም ከ300 በላይ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮሚሽነር አበረ ገልጸዋል። ግለሰቦችን ወደ ህግ ለማቅረብ በተደረገው እንቅስቃሴም ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ።
የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና ማጣራቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን የተናገሩት ኮሚሽነሩ፥ ከተያዙት መካከል ጉዳያቸው ተጣርቶ የሚለቀቁ እንደሚኖሩም አመላክተዋል።
በነባሮች እና አዲስ በሰለጠኑት የልዩ ኃይል አባላት መካከል ልዩነት እንዳለ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ክልሉ ጠንካራ የጸጥታ ኃይል እንዳይኖረው የተሰራ የፖለቲካ ሴራ እንጂ ምንም አይነት ልዩነት እንደሌለም ነው የተናገሩት።
ህጋዊ ትጥቅ ያላቸውን ግለሰቦች ትጥቅ የማስፈታት ስራ ተጀምሯል እየተባለ የሚሰራጨው ወሬ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ ታስቦ የሚናፈስና ከእውነት የራቀ አሉባልታ መሆኑንም ኮሚሽነር አበረ ተናግረዋል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ ስጋት ውስጥ እንዳይገባም መልዕክት ያስተላለፉት ኮሚሽነሩ ፥ ክልሉ ሙሉ በሙሉ #በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
Via #EPA
🗞ቀን 22/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia