#update የአማራ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ህዝቦች የጋራ የሰላምና የልማት መድረክ በአሶሳ ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ። የአማራ ብሄራዊ ክልል እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት መድረክ ባለፉት ዓመታት በሁለቱ ክልል #ከፍተኛ አመራሮች እየተመራ መቆየቱ ይታወቃል። የሁለቱ ክልል የጋራ የሰላምና የልማት መድረክ ነገ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ የሚካሄድ ይሆናል። በመድረኩ የሁለቱ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን የሚገኙ ሲሆን በጋራ ስምምነቱ የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም ለቀጣይ ስራዎች የጋራ ውይይት ይካሄዳል። የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችን ያካተተ የሉኡካን ቡድን ዛሬ አሶሳ ከተማ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
Via የክልሉ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via የክልሉ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#REPOST አዲሶቹ የብር ኖቶች አይነት እና የደህንነት መጠበቂያ ምልክቶች ፦ ተከታታይ ቁጥሮች ፦ የገንዘቡ ቁጥሮች በሚያጎላ ማሽን ሲታዩ ከጥቁር ወደ አረንጓዴ ፍሎረሰንት ቀለም ይለወጣሉ። ማየት ለተሳናቸው እውቅና ምልክት ፦ የብሩን ዋጋ የሚገልፅ ማየት የተሳናቸው በእጅ ዳሰሳ ማወቅ የሚችሉበት የደህንነት መጠበቂያ ምልክት አለው። ጎርባጣ መስመሮች ፦ የባንክ ኖቱ ሲዳሰስ የመጎርበጥ ስሜት እንዲሁም…
#ከፍተኛ_ጥንቃቄ_እያደረጋችሁ !!
በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ በአሽፋ ባህራ ደረዋ ቀበሌ ሃሰተኛ 80 ሺህ ባለ መቶ የብር ኖት እጅ ከፈንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት፥ እንጅባራ ነዋሪ የሆኑት አቶ ያረጋል ጥላሁን እና አቶ ግርማው ታፈረ በቀን 28/01/2013 ዓ/ም ከቀኑ 12፡00 አሽፋ ገበያ ሃሰተኛ ብር ይዘው ሲንቀሳቀሱ የተገኙ መሆናቸውን ገልጿል፡፡
በአሁን ሰዓት አንድ ግለሰብ ከ 15,000 ብር በላይ ይዞ መገበያየት ስለማይቻል እነሱ የሚገዙት እቃ 80 ሺህ ብር ስለሆነባቸው በእጅ እንስጥ ብለው በባጃጅ ወጥተው ከመንገድ እንደተቀባበሉት ተገልጿል።
60,000 ብሩ ወዲያውኑ የተያዘ ሲሆን 20,000 ብሩ በዛሬ 29/01/2013 ዓ.ም ደላላ የሆነው ሙሉቀን አለነ የተባለ ግለሰብ አምጥቶ አስረክቧል ተብሏል።
ሁሉም ማህበረሰብ በአሁኑ ሰዓት አዲስ የተቀየረውን የብር ኖት እንዳይጭበረበር ስለብር ኖቶቹ በደንብ አውቆ መንቀሳቀስ እንዳለበት መልዕክት ተላልፏል፡፡
(Guagusa Shikudad Communication)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ በአሽፋ ባህራ ደረዋ ቀበሌ ሃሰተኛ 80 ሺህ ባለ መቶ የብር ኖት እጅ ከፈንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት፥ እንጅባራ ነዋሪ የሆኑት አቶ ያረጋል ጥላሁን እና አቶ ግርማው ታፈረ በቀን 28/01/2013 ዓ/ም ከቀኑ 12፡00 አሽፋ ገበያ ሃሰተኛ ብር ይዘው ሲንቀሳቀሱ የተገኙ መሆናቸውን ገልጿል፡፡
በአሁን ሰዓት አንድ ግለሰብ ከ 15,000 ብር በላይ ይዞ መገበያየት ስለማይቻል እነሱ የሚገዙት እቃ 80 ሺህ ብር ስለሆነባቸው በእጅ እንስጥ ብለው በባጃጅ ወጥተው ከመንገድ እንደተቀባበሉት ተገልጿል።
60,000 ብሩ ወዲያውኑ የተያዘ ሲሆን 20,000 ብሩ በዛሬ 29/01/2013 ዓ.ም ደላላ የሆነው ሙሉቀን አለነ የተባለ ግለሰብ አምጥቶ አስረክቧል ተብሏል።
ሁሉም ማህበረሰብ በአሁኑ ሰዓት አዲስ የተቀየረውን የብር ኖት እንዳይጭበረበር ስለብር ኖቶቹ በደንብ አውቆ መንቀሳቀስ እንዳለበት መልዕክት ተላልፏል፡፡
(Guagusa Shikudad Communication)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia