TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SNNPR

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በደ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግሥት 170 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ መካከል ሶስት (3) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በክልሉ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 16 ደርሷል።

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦

ታማሚ 1 - የ38 ዓመት ወንድ ከሀዋሳ ፤ የረጅም ርቀት አሽከርካሪ።

ታማሚ 2 - የ66 ዓመት ወንድ ከሀዋሳ ፤ የውጭ ሀገር ጉዞና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የታወቀ ግንኙነት #የሌላቸው

ታማሚ 3 - የ28 ዓመት ወንድ ከሀዋሳ ፤ የረጅም ርቀት አሽከርካሪ።

ሶስቱም በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው ግለሰቦች ሀዋሳ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ መደረጉን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 1,205 ደርሰዋል! 

በአዲስ አበባ ከተማ እስከ ዛሬ ግንቦት 27/2012 ዓ/ም ድረስ በተደረጉ የላብራቶሪ ምርመራዎች 1,205 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል።

ባለፉት 24 ሰዓት ቫይረሱ የተገኘባቸው 123 ሰዎች ሲሆኑ ከነዚህ መካከል 8 ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው፣ 12 ሰዎች በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር የታወቀ ግንኙነት ያላቸው የተቀሩት 103 ሰዎች የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክም ሆነ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #የሌላቸው ናቸው።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በአዲስ አበባ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው አንድ መቶ ሃያ ሶስት (123) ሰዎች ክፍለ ከተማ ፦

• አዲስ ከተማ - 50 ሰዎች
• ልደታ - 4 ሰዎች
• ጉለሌ - 16 ሰዎች
• ቦሌ - 21 ሰዎች
• ኮልፌ ቀራኒዮ - 6 ሰዎች
• አራዳ - 3 ሰዎች
• ቂርቆስ - 10 ሰዎች
• የካ - 3 ሰዎች
• ንፋስ ስልክ ላፍቶ - 2 ሰዎች
• አቃቂ ቃሊት - 0
* አድራሻቸው በመጣራት ላይ ያለ - 8 ሰዎች

አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ 1,205 ሰዎች ክፍለ ከተማ እንደሚከተለው ቀርቧል ፦

• አዲስ ከተማ - 355 ሰዎች
• ልደታ - 180 ሰዎች
• ጉለሌ - 157 ሰዎች
• ቦሌ - 120 ሰዎች
• ኮልፌ ቀራኒዮ - 116 ሰዎች
• አራዳ - 51 ሰዎች
• ቂርቆስ - 51 ሰዎች
• የካ - 49 ሰዎች
• ንፋስ ስልክ ላፍቶ - 43 ሰዎች
• አቃቂ ቃሊት - 29
* አድራሻቸው በመጣራት ላይ ያለ - 54 ሰዎች

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia