አውቶብሱ የተገለበጠው የሰሌዳ ቁጥሩ ይፋ ያልተደረገ ኮድ 3 አ/አ መኪና ለመሸሽ ሲሞክር ነው!
እስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ጀርባ በሚገኝው ድልድይ ውስጥ የመውደቅ አደጋ የገጠመው የከተማ አውቶብሱ ምክንያት ለጊዜው የሰሌዳ ቁጥር ይፋ ያልተደረገ ኮድ 3 አ.አ መኪና ለመሸሽ ሲል እንደሆነ የእሳት እና ድንገተኛ አደጋዎች የኮምንኬሽን ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለሽገር ራድዮ አስረድተዋል።
አውቶብሱ የተለመደ የመስመር ቁጥር ያልተሰጠው አዲስ ስምሪት እንደሆነም ታውቋል። መነሻውንም ከሽሮሜዳ አድርጎ ወደ ካዛንችስ እየሄደ እንደነበርም ነው ባለሙያው የተናገሩት። አደጋው ያጋጠመው አንበሳ የከተማ አውቶብስ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- አ/አ 68377 እንደሆነ ታውቋል። በዚሁ አደጋም 31 ሰዎች ብርቱ ጉዳት እንደገጠማቸው ተሰምቷል።
ካሰቡበት ለመድረስ #በአውቶብሱ ተሳፍረው አደጋው ያገኛቸው ኢትዮጵያውያንም ወደ ጥቁር አንበሳ ዘውዲቱ እና አቤት ሆስፒታል መወሰዳቸውን ባለሙያው ተናግረዋል። በደረሰው አደጋ እስካሁን የ2 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል። የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር ይችላል ያሉት የኮምንኬሽን ባለሙያው ናቸው።
Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ጀርባ በሚገኝው ድልድይ ውስጥ የመውደቅ አደጋ የገጠመው የከተማ አውቶብሱ ምክንያት ለጊዜው የሰሌዳ ቁጥር ይፋ ያልተደረገ ኮድ 3 አ.አ መኪና ለመሸሽ ሲል እንደሆነ የእሳት እና ድንገተኛ አደጋዎች የኮምንኬሽን ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለሽገር ራድዮ አስረድተዋል።
አውቶብሱ የተለመደ የመስመር ቁጥር ያልተሰጠው አዲስ ስምሪት እንደሆነም ታውቋል። መነሻውንም ከሽሮሜዳ አድርጎ ወደ ካዛንችስ እየሄደ እንደነበርም ነው ባለሙያው የተናገሩት። አደጋው ያጋጠመው አንበሳ የከተማ አውቶብስ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- አ/አ 68377 እንደሆነ ታውቋል። በዚሁ አደጋም 31 ሰዎች ብርቱ ጉዳት እንደገጠማቸው ተሰምቷል።
ካሰቡበት ለመድረስ #በአውቶብሱ ተሳፍረው አደጋው ያገኛቸው ኢትዮጵያውያንም ወደ ጥቁር አንበሳ ዘውዲቱ እና አቤት ሆስፒታል መወሰዳቸውን ባለሙያው ተናግረዋል። በደረሰው አደጋ እስካሁን የ2 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል። የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር ይችላል ያሉት የኮምንኬሽን ባለሙያው ናቸው።
Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
912 ሺህ 292 ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል ተዘዋውረዋል!
በ2011 ዓ/ም የ10ኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው ወደ ቀጣይ ክፍል የተዘዋወሩት 912 ሺህ 292 ተማሪዎች ሲሆኑ ከተዘዋወሩት ተማሪዎች መካከል 750 ሺ 174 ወንዶች ናቸው፤ 162 ሺ 118 ተማሪዎች ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል። በአጠቃላይ ወደ 11ኛ ክፍል ከተዘዋወሩ ተማሪዎች መካከል የሴቶች ድርሻ 17.77 በመቶ መሆኑን ከአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ የባለፈው አመት የመደበኛና የማታ ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ ለወንዶች 2.71 እና ለሴቶች 2.57 እንደበር ይታወሳል፡፡ በግል ለተፈተኑት ወንዶች 3.43 እና ለሴቶች 3.14 የማለፊያ ውጤት ሆኖ መመዝገቡን የኤጀንሲው መረጃ ያመለክታል፡፡
Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በ2011 ዓ/ም የ10ኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው ወደ ቀጣይ ክፍል የተዘዋወሩት 912 ሺህ 292 ተማሪዎች ሲሆኑ ከተዘዋወሩት ተማሪዎች መካከል 750 ሺ 174 ወንዶች ናቸው፤ 162 ሺ 118 ተማሪዎች ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል። በአጠቃላይ ወደ 11ኛ ክፍል ከተዘዋወሩ ተማሪዎች መካከል የሴቶች ድርሻ 17.77 በመቶ መሆኑን ከአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ የባለፈው አመት የመደበኛና የማታ ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ ለወንዶች 2.71 እና ለሴቶች 2.57 እንደበር ይታወሳል፡፡ በግል ለተፈተኑት ወንዶች 3.43 እና ለሴቶች 3.14 የማለፊያ ውጤት ሆኖ መመዝገቡን የኤጀንሲው መረጃ ያመለክታል፡፡
Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia