TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UPDATE

- ዛሬ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ለሦስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ወደ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች አቅንተዋል።

- ዶ/ር ዐቢይ በአቡዳቢ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼህ አብደላ ቢን ዛይድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

- ጠ/ሚ ዶ/ር በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ የተለያዩ አገራት ከተወጣጡ 300 የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር በዱባይ ውይይት አካሂደዋል።

#EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድም ሰው የለም!

በአፍሪካ እስከ የካቲት 6 ቀን 2012 ከቀኑ 8 ሰዓት ድረስ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድም ሰው አለመኖሩን በአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማእከል (CDC) ዳይሬክተር ዶ/ር ጆን ንኬንጋሶንግ ተናግረዋል። ዳይሬክተሩ ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በአፍሪካ እስከ የካቲት 6 ቀን 2012 ከቀኑ 8 ሰዓት ድረስ በኮሮና ቫይረስ የተረጠሩ 51 ሰዎች እንደነበሩ ተናግረው፣ ሁሉም ከቫረሱ ነፃ መሆናቸው በምርመራ ተረጋግጧል ብለዋል፡፡ የኮሮና ቫይረስ መንስኤ በንድፈ ሐሳብ ደረጃ የውኃ ድብ ወይም የሌሊት ወፍ ሊሆን ይችላል ከማለት ውጭ በትክክል መንስኤው እስካሁን አለመታወቁን ጠቁመዋል፡፡

#EBC
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot