TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ADAMA

"አዳማ ዛሬ ከነጋ ጀምሮ በሁሉም አቅጣጫ #ሠላም ነው። ሠላማዊ ህይወት እንድቀጥል ህዝባችን በማህበራዊ ሚድያ በማይታወቁ እና አከባቢው ላይ በማይገኙ ሰዎች የሚረጨውን የክፍፍል ወሬ ችላ በማለት ለሠላም ሊተጋ ይገባል።" ባይሳ(ቲክቫህ ቤተሰብ) ከአዳማ ፖስታቤት አከባቢ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA

የአዳማ ከተማ የዛሬ ውሎ ፍፁም የተረጋጋና ሰላማዊ ነው። የንግድ ተቋማት ወደስራቸው ተመልሰዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደቀደመው ሁኔታ እየተመለሰ ይገኛል። አብዛኛው የትምህርት ተቋማት ግን ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ተማሪዎች አልተገኙም። የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደሚሉት በተማሪዎች መካከል ግጭት እንዳይፈጠር በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት አላኩም ብለዋል። በትላናንትናው ዕለት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከተማይቱ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷን ገልፆ በቀጣይ ቀናትም ትምህርት ቤቶች ወደ ስራ ይመለሳሉ ሲል ገልጿል።

PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia