TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኦነግ‼️

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በምርጫ ቦርድ እንዲመዘገብ የቀረበለትን ጥያቄ #አልቀበልም አለ መባሉን #አስተባበለ። ፓርቲው ለምርጫ ቦርድ የምዝገባ ጥያቄ አቅርቤያለሁ ብሏል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ #ቀጀላ_መርዳሳ በአርትስ ቴሌቪዠን ላይ ቀርበው እንደተናገሩት ኦነግ ምርጫ ቦርድ ቀርቤ አልመዘገብም አለ በሚል የሚናፈሱ መረጃዎች #ትክክል_አይደሉም ብለዋል። እንደአቶ ቀጀላ ገለጻ ኦነግ ምዝገባ ለማካሄድ ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቅርቧል። ነገር ግን የፓርቲዎች ምዝገባ መመሪያ ላይ የሰፈሩት ቅድመ ሁኔታዎች ድርጅቱ ለምርጫ ከሚያደርገው ዝግጅት ጊዜ መጣበብ እና ከድርጅቱ ታሪካዊ አመጣጥ ጋር ሊጣጣሙለት አልቻሉም።

የ45 ዓመታት የምስረታ ታሪክ ያለው ኦነግ በአዲስ ሁኔታ 1500 ሰዎችን አስፈርሞ ለምዝገባ እንዲቀርብ መጠየቁ ድርጅቱን እንደአዲስ የመቁጠር ያህል ነው ያሉት አቶ ቀጀላ ኦነግን በአዲስ አባላትና ደጋፊዎች ማዋቀርም የመስራች አባላቱን ታሪክ መፋቅ ነው ብለዋል።

ኦነግ በአሁኑ ወቅት ወደኢትዮጵያ የመጣው በፖለቲካ ውሳኔ መሆኑን የተናገሩት ከፍተኛ አመራሩ ይህም በይፋ እውቅና የተሰጠው ድርጅት መሆኑን ይመሰክራል ነው ያሉት።

ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍2
ዓምዶም አልታሰረም...

"ወዳጆቼ ዓምዶም ታስረዋል የሚለው መረጃ #ትክክል_ኣይደለም። ኣልታሰርኩም። ስላሰባቹልኝ ኣመሰግናለው!" ዓምዶም በፌስ ቡክ ገፁ ላይ እንዳሰፈረው።

@tsegabwolde @tkivahethiopia
1
አፈ ጉባኤዋ ይቅርታ ጠየቁ!

የደቡብ ክልል ምክር ቤት #ዋና_አፈ_ጉባኤ የምክር ቤቱ አባላት #ይቅርታ ያድርግልኝ ሲሉ በይፋ ጠየቁ። ዋና አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሄለን ደበበ ዛሬ ረፋድ ላይ የተጀመረውን የክልሉን አምስተኛ ዙር መደበኛ ጉባኤ በንግግር ሲከፍቱ ላለፉት አስራ አንድ ወራት የምክር ቤቱን መደበኛ ጉባኤዎች ባለመጥራቴ የተከበሩ የምክር ቤት አባላት ይቅርታ ያድርጉልኝ ሲሉ ተማፅነዋል።

የህዝብ ውክልና ያለው ምክር ቤት በየጊዜው ማከናወን የነበረበትን ስብሰባ አለማድረጉ በየትኛውም መመዘኛ #ትክክል አይደለም ያሉት ዋና አፈ ጉባኤዋ በቀጣይ ተመሳሳይ #ስህተት እንደማይደገም በምክር ቤቱ ፊት ቃል እገባለሁ ብለዋል። በእርግጥ እንደምክንያት ማቅረብ ባይቻልም ምክር ቤቱ ማድረግ የነበረበትን መደበኛ ጉባኤዎች ሳያካሂድ የቀረው ክልሉ አጋጥሞት ከነበረው ነባራዊ ሁኔታ የተነሳ መሆኑን አፈ ጉባኤዋ ተናግረዋል።

የደቡብ ክልል ምክር ቤት በዓመት #አራት መደበኛ ጉባኤዎችን ማድረግ የሚገባው ቢሆንም ባለፈው የጥቅምት ወር የመጀመሪያውን ስብስባ ካደረገ ወዲህ ዳግም ሳይሰበሰብ ነው የበጀት ዓመቱ የተጠናቀቀው። በዚህም ምክንያት የክልሉ ዓመታዊ በጀት እስከአሁን ባለመፅደቁ የአስፈጻሚ ቢሮዎች ከሀምሌ 1 2012 ዓም ጀምሮ መደበኛ ስራዎቻቸውን በምክር ቤት ባልጸደቀ በጀት ሲያከናውኑ ቆይተዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia