TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የዋጋ ጭማሪ...

በአዲስ አበባ ከተማ በመሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ተከትሎ የከተማው አስተዳደር ጥናት በማድረግ እርምጃ ሊወስድ መዘጋጀቱን ገለፀ። በተለይም በአትክልት ምርቶች ላይ የታየው ጭማሪ አሳሳቢ እንደሆነ በአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ የንግድ ቁጥጥርና ክትትል የሥራ ሒደት መሪ ካሳሁን በየነ ገልጸዋል። በአገሪቱ በነበረው #የሰላም_መደፍረስ ምክንያት የአትክልት አቅራቢዎች በበልግ ወቅት በሙሉ አቅማቸው ያለማምረታቸው በክረምት ወቅት የሚያጋጥመውን የምርት እጥረት አባብሶታል ብለዋል። በተለይም መቂ ከተማን ጨምሮ በመስኖ ምርት የከተማዋን የአትክልት አቅርቦት በሚሸፍኑ አካባቢዎች ላይ የተፈጠረው ጫና የተወሰነ የምርት እጥረት አምጥቷል ቢባልም ላለፉት ኹለት ሳምንታት የታየው ጭማሪ ግን ሰው ሰራሽ ሊሆን እንደሚችል ካሳሁን ሥጋታቸውን ገልጸዋል።
.
.
“መንግሥት የገበያ ዋጋን ለማውጣት እና ለማስገደድ ሕጉ አይፈቅድለትም፣ ነገር ግን የሕዝብ ኑሮ ላይ ጫና ለመፍጠር እና ያለአግባብ ለመበልፀግ የሚደረግ አሻጥር ላይ ግን ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ጥናታችን አጠናቀናል” አቶ ካሳሁን

Via አዲስ ማለዳ
@tsegabwolde @tikvahethiopia