#update ደብዛው የጠፋው ጋዜጠኛ⬇️
የቱርክ ፕሬዚዳንት #ጣይብ_ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ #ሳልማን_ቢን አብዱልአዚዝ ደብዛው በጠፋው ጋዜጠኛ ጉዳይ ላይ በስልክ #ተወያዩ።
ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከሁለት ሳምንት በፊት ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኮንስላ ጽህፈት ቤት ጉዳይ #ሊያስፈፅም እንደገባ ደብዛው ከጠፋ 13 ቀናት ተቆጥረዋል።
የቱርክ ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ ሳልማን ትናንት ሌሊት በስልክ ባደረጉት ውይይት የጋዜጠኛው መጥፋት ጉዳይ አጀንዳቸው ነበር ተብሏል።
ኤርዶሃን በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ላይ ጥምር ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ እንዲካሄድ በአፅንኦት መናገራቸው ተሰምቷል።
ካሾጊ በሳዑዲ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በነበረበት ወቅት 10 ሳዑዲዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት በሁለት አውሮፕላኖች ወደ ኢስታንቡል በማምራት ጽህፈት ቤቱን በተመሳሳይ ቀን መጎብኘታቸውን የቱርክ ፖሊስ መረጃዎች ያሳያሉ።
የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ አምደኛ የሆነው የሳዑዲ ዜግነት ያለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ የት እንደገባ አለመታወቁን ተከትሎ ቱርክ፣ አሜሪካ እና ብሪታኒያ ከሳዑዲ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቱርክ ጋዜጠኛው #መገደሉን የሚያሳዩ መረጃዎችን አግኝቻለሁ እያለች ነው።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳሉት ጋዜጠኛው በቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ውስጥ መገደሉ ከተረጋገጠ ሳዑዲ ከባድ #ቅጣት ይጠብቃታል ብለዋል።
ይህን ተከትሎም ሳዑዲ በሰጠችው ምላሽ ማንኛውም ሀገር በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ሀሰተኛ ውንጀላ የሚያቀርብ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሚያስብ ሀገር ካለ የአፀፋ ምላሽ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች።
ምንጭ፦ አናዶሉና ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቱርክ ፕሬዚዳንት #ጣይብ_ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ #ሳልማን_ቢን አብዱልአዚዝ ደብዛው በጠፋው ጋዜጠኛ ጉዳይ ላይ በስልክ #ተወያዩ።
ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከሁለት ሳምንት በፊት ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኮንስላ ጽህፈት ቤት ጉዳይ #ሊያስፈፅም እንደገባ ደብዛው ከጠፋ 13 ቀናት ተቆጥረዋል።
የቱርክ ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ ሳልማን ትናንት ሌሊት በስልክ ባደረጉት ውይይት የጋዜጠኛው መጥፋት ጉዳይ አጀንዳቸው ነበር ተብሏል።
ኤርዶሃን በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ላይ ጥምር ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ እንዲካሄድ በአፅንኦት መናገራቸው ተሰምቷል።
ካሾጊ በሳዑዲ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በነበረበት ወቅት 10 ሳዑዲዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት በሁለት አውሮፕላኖች ወደ ኢስታንቡል በማምራት ጽህፈት ቤቱን በተመሳሳይ ቀን መጎብኘታቸውን የቱርክ ፖሊስ መረጃዎች ያሳያሉ።
የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ አምደኛ የሆነው የሳዑዲ ዜግነት ያለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ የት እንደገባ አለመታወቁን ተከትሎ ቱርክ፣ አሜሪካ እና ብሪታኒያ ከሳዑዲ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቱርክ ጋዜጠኛው #መገደሉን የሚያሳዩ መረጃዎችን አግኝቻለሁ እያለች ነው።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳሉት ጋዜጠኛው በቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ውስጥ መገደሉ ከተረጋገጠ ሳዑዲ ከባድ #ቅጣት ይጠብቃታል ብለዋል።
ይህን ተከትሎም ሳዑዲ በሰጠችው ምላሽ ማንኛውም ሀገር በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ሀሰተኛ ውንጀላ የሚያቀርብ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሚያስብ ሀገር ካለ የአፀፋ ምላሽ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች።
ምንጭ፦ አናዶሉና ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
❤1
ሳውዲ አረቢያ አመነች‼️ሳውዲ አረቢያ ከ17 ቀናት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጂ በኢስታንቡል ቆንስላዋ ውስጥ በተፈጠረ አምባጓሮ #መገደሉን አመነች። ከዚህ ጋር በተያያዘ የደህንነት መስሪያ ቤቷን ም/ኅላፊ ማባረሯን አስታውቃለች።
©BBC
@tsegawolde @tikvahethiopia
©BBC
@tsegawolde @tikvahethiopia
የአፋር ውሎ...🔝
በአፋር ክልል አንድ ታዳጊ በመከላከያ ሰራዊት አባላት #መገደሉን ተከትሎ #ፍትህ የጠየቁ ወጣቶች በገዋኔ፣ በረሃሌና አዋሽ አካባቢዎች መንገዶችን ዘግተው ውለዋል። በዚህም አዲስ አበባን ከጅቡቲና የትግራይ ክልልን ከአዲስ አበባ የሚያገናኘው መንገድ ለሰዐታት ተዘግቶ ነበር።
Via #ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአፋር ክልል አንድ ታዳጊ በመከላከያ ሰራዊት አባላት #መገደሉን ተከትሎ #ፍትህ የጠየቁ ወጣቶች በገዋኔ፣ በረሃሌና አዋሽ አካባቢዎች መንገዶችን ዘግተው ውለዋል። በዚህም አዲስ አበባን ከጅቡቲና የትግራይ ክልልን ከአዲስ አበባ የሚያገናኘው መንገድ ለሰዐታት ተዘግቶ ነበር።
Via #ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia