TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወላይታ ሶዶ🔝

መንግስት በወላይታ ሶዶ ከተማ ዙሪያ ህገወጥ ናቸው #ባላቸው ግንባታዎች ላይ የማፍረስ #እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ የተፈጠረው አለመረጋጋት ረገብ ብሏል። ከተማዋም ወደቀደመ #ሰላማዊ እንቅስቃሴዋ እየተመለሰች ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኒውዚላንድ🔝

በኒውዚላንድ #ክሪስትቸርች ከተማ ሁለት መስጊዶች ላይ ጥቃት በመፈፀም 49 #ሰላማዊ ዜጎችን ህይዎት በማጥፋት ከተጠረጠሩ ግለሰቦች ውስጥ አንደኛው በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቧል።

ድርጊቱን የፈፀመው ተጠርጣሪ ብሬንቶን ታራንት የሚባል ሲሆን፥ በዜግነትም አውስትራሊያዊ መሆኑ ነው የተገለፀው።

የ28 ዓመቱ ብሬንቶን ታራንት በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት የቀረበውም በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ነው ተብሏል።

ፅንፈኛ #ቀኝ_ዘመም_አሸባሪ የተባለው ተጠርጣሪ #ብሬንቶን_ታራንት ፍርድ ቤቱ ያቀረበበትን ክስ በዝምታና በአርምሞ አድምጧል ነው የተባለው ።

ፍርድ ቤቱ የተጠርጣሪውን የይግባኝ መብት በመከልከል ጉዳዩን በድጋሜ ለመመልከት ለፊታችን ሚያዝያ 5 ቀጠሮ ይዟል።

በሽብር ጥቃቱ የተጠረጠሩ ሁለት ተጨማሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ፥ ሁለቱም ከዚህ በፊት በምን አይነት የወንጀል ተጠርጥረው  ፍርድ ቤት ቀርበው የማያውቁ መሆኑ ተገልጿል።

የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር #ጃሲንዳ አርደርን ድርጊቱን የሽብር ጥቃት በማለት ያወገዙ ሲሆን፥ በጥቃቱ የተጎዱ ዜጎችን ማንነት  የመለየት ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠርጣሪዎች  ድርጊቱን ለመፈፀም የተጠቀሙበት #መሳሪያ ዘመናዊና የተሻሻለ መሆኑን በመጥቀስ፥ የፀጥታ አካላት ባደረጉት #እርብርብ በፍጥነት በቁጥጥር ስር በማዋል የሚደርሰውን እልቂት ለመታደግ ተችሏል ብለዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia