TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለገጣፎ ለገዳዲ‼️

በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር ሕገወጥ ናቸው ተብለው የፈረሱ ቤቶች ጉዳይ የሰሞኑ መነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከኦሮሚያ ክልል የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው እስከ ትናንት ምሽት ድረስ 3,800 ቤቶች ፈርሰዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ቤቶቹ #በሕገወጥ መንገድ የተሰሩ በመሆናቸው የወሰድኩት #እርምጃ ሕግን የማስከበር ሥራ ነው ብሏል፡፡

ነዋሪዎች በበኩላቸው ከ10 እስከ 19 ዓመት ቤት ገንብተው መኖራቸውን የአፈር ግብር ለመንግሥት እንደሚከፍሉና ውሃና መብራትን ጨምሮ መሰረተ ልማት የከተማ አስተዳደሩ እንዳሟላላቸው ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን መናገራቸው ይታወቃል፡፡ ነዋሪዎች ቤታችን በመፍረሱ ጎዳና ላይ ወድቀናል የሚል #እሮሮ እያሰሙ ነው፡፡

የኦሮሚያ ክልል የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ሃላፊውን ዶክተር #ሚልኬሳ_ሚደግሳ ሸገር 102.1 ራድዮ በጉዳዩ ዙሪየ አነጋግሯቸዋል።

Via Sheger FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia